
Natnael Mekonnen
@NatnaelMekonne7 • 383,875 subscribers
No one can Judge me only God can Judge me ! https://t.co/peGFd40VeL https://t.co/s40zMIggYn
Shorts
Videos

ከሞት የተረፉት የአርሚ 13 ታጋዮች እንዲሄዱ በታዘዙት መሠረት ሱዳን ገብተዋል ኮረኔል ምግቤ ሃይሌ ምግቤ ይሄንን ያለው የምዕራብ ግንባር የጦር አመራሮችን ሸራሮ ከተማ ውስጥ በሰበሰበበት ቀን(ሃሙስ)ነው። እሱ ከተናገራቸው የሰይጣኖች ስብስብ የሆነው ብልፅግና በአርሚ 13 ሰራዊታችን ላይ ከባድ ጭፍጨፋ ፈፅሟል ( የሸራሮውን የድሮን ጥቃት ማለቱ ነው) መስዋዕትነት የከፈሉት እነዚህ የአርሚ 13 አባላት ከቀደሙ ታጋዮች የተሰጣቸውን አደራ እየፈፀሙ የነበሩ ናቸው። ይህ እኛን አያንበረክከንም ፤ ምክንያቱም እኛ ትግሬዎች ነን በጣም ደስ የሚለው ነገር ግን ከጥቃቱ የተረፉት የአርሚ 13 አባላት የታዘዙትን ፈፅመዋል ወደተባሉበት ቦታ ደርሰዋል ( ሱዳን ገብተዋል ማለቱ ነው። ሱዳን ከገቡ በኋላ ያጋጠማቸውን ነገር ግን አልተናገረም የሸራሮ ህዝብ በጥቃቱ የተገደሉትን አባላቶቻችንን በክብር ስለቀበራችኋቸው እናመሰግናለን።
Natnael Mekonnen12,004 views • 13 days ago
3:22
Sensitive content
This media may contain sensitive content.

❝የትግራይ እናቶች ሆይ ልጆቻችሁን ከህወሓት የሞት ድግስ ታደጉ❞ ከአር.ኤስ.ኤፍ የተላለፈ መልዕክት በሀገር ውስጥ ጦርነት ለመክፈት እየተጣደፈ የሚገኘው ፀረ ህዝብ የሆነው አሸባሪው ህወሓት የትግራይ ወጣቶችን ለሱዳኑ አል ቡርሀን በዶላር እየሸጠ ለእልቂት እየዳረጋቸው ነው። በአሁኑ ጊዜ በርካታ የትግራይ ወጣቶች በሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሃይል (RSF) በምስሉ ላይ እንደሚታየው የህወሓት ታጣቂ እየተማረኩ ነው።ታዲያ ይህ ምስሉ ላይ ከሚታይ ወጣት ፊት ላይ እና ከሚናገራቸው ነገሮች በርካታ ሀሳቦችን መረዳት እና ማንበብ ይቻላል።የመጀመሪያው ህወሓት ታጣቂዎቹን አዕምሯቸው በትክክለኛው መንገድ ማሰብ እንዳይችል እና ወደ ጦር ግንባር ሳያስቸግሩ እንዲገቡ በከፍተኛ ሁኔታ አደንዛዥ የሆኑ እፆችን ምግብ ጋር እየቀላቀለ እንዲሁም በመርፌ ወግቶ በመስጠት ሱሰኛ እንደሚያረጋቸው ነው። በርግጥ ይህ ታጣቂዎችን በአደንዛዥ እፅ የማደንዘዝ ሁኔታ በሰሜኑ ጦርነት ጊዜም በሰፊው ህወሓት ሲያደርግ የነበረው ነው።ምስሉ ላይ የሚታየው ወጣትም በከፍተኛ ሁኔታ አደንዛዥ እፅ እንዲጠቀም ተደርጎ አዕምሮውን እንዲስት ህወሓት አድርጎ እሳት ውስጥ ያለፍቃዱ እንደከተቱት ፊቱ ላይ በግልጽ የሚታይ ነው።ሁለተኛው ደግሞ ህወሓት እድሜያቸው ለጦርነት ያልደረሱ ህፃናትን ለዶላር እና ለስልጣን ሲል ወደ ጦር ግንባር በግድ መልምሎ እንደሚያስገባ ነው።ምክንያቱም ደግሞ ምስሉ ላይ የሚታየው ታጣቂ ገና እድሜው ለጦርነት እንዳልደረሰ እና በህወሓት ታጣቂዎች በግድ ከትምህርት ቤት በግድ ታፍሶ ወደ ሱዳን እንደመጣ ከተማረከ በኋላ ለ RSF ታጣቂዎች ሲናገር ስለተደመጠ ነው። ሶስተኛው ደግሞ ህወሓት ከፍተኛ ዶላር ከሱዳኑ አል ቡርሀን ቢያገኝም ይህን ዶላር ለግል ጥቅሙ ከማዋል ባለፈ ሱዳንም ሆነ ትግራይ ውስጥ ለሚገኙ ታጣቂዎች በቂ ምግብ እና ውሀ እንደማያቀርብላቸው ነው።ምክንያቱም ይህ የተማረከ ወጣት ምግብ እና ውሀ ፍለጋ ከህወሓት አርሚ 70 ካምፕ ወጦ በጠፍበት ጊዜ በመማረኩ ነው።ለዚህም ነው ምስሉ ላይ እንደሚታየው ሰውነቱ ላይ የወረሩትን ዝምቦች ጭምር መከላከል እስኪያቅተው ድረስ በርሀብ እና በውሀ ጥም ምክንያት እራሱን ስቶ እና ተዝለፍልፎ የሚታየው። ከዚህ ምስል ላይ ዋናው ጉዳይ ግን ምስሉ ላይ የሚታየውን የህወሓት ታጣቂ የማረኩት የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሃይሎች (RSF) ለትግራይ እናቶች እና ለትግራይ ህዝብ ያስተላለፍት መልዕክት ነው።ይህ መልዕክትም ❝የትግራይ እናቶች ሆይ ህወሓት ለገንዘብ ብሎ ልጆቻችሁን የእናንተ ጉዳይ ወዳልሆነው የሱዳን ጦርነት መላኩን አስቁሙ። ብዙ ወጣቶች በከንቱ እየረ'ገፉ ነው። እኛ ይሄንን ወጣት ልጅ ማርከነዋል። በፍጹም አንገድለ'ውም፤ አካላዊ ጥቃትም አናደርስበትም። እኛ ሙስሊሞች ነን፤ ኃይማኖታችን በምርኮ የተያዘን ወታደር ግደ'ሉ ወይም አጎሳቁሉ ብሎ አያስተምርም፤ ስለዚህ ይሄንን ወጣት ምንም አናደርገውም አታስቡ❞ በማለት በህወሓት ምክንያት የትግራይ ወጣት ሱዳን ውስጥ እንደ ጭድ መቃጠሉ መቆም አለበት ብለዋል። ይህ እጅግ የሚያሳዝን ክስተት ነው ላለፉት አመታት የህወሃት አመራሮች በርካታ የትግራይ ወጣቶችን በሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ልክ ምስሉ ላይ እንደሚታየው ታጣቂ በግድ እንዲሳተፉ በማድረግ በርካታ ወጣቶችን ለሞት ዳርጓል አሁንም ድረስ ወጣቱ በማያገባው እና በማያውቀው ጦርነት ሰላባ መሆኑ ስለቀጠለ ይህ ደግሞ መቆም አለበት።
Natnael Mekonnen13,193 views • 1 month ago

#አፈትላኪ #leaked በልዩ ሃይሉ ስም ሀገሪቷን የብጥብጥ ቀጠና ለማድረግ እየሰሩ የሚገኙት እነ መስከረም አበራ እና ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ በስልክ ያደረጉትን ንግግር ተመልከቱ! እነዚህ ሰዎች ስለ ህገ-ወጥ ገንዘብ ዝውውር፣ ለምን ልዩ ሃይሉ በሰላም መሳሪያውን ያወርዳል እያሉ በአማራ ህዝብ ላይ 👉የባንዳነት ተግባር ሲፈፅሙ ተመልከቱ። በንግግራቸው ካነሷቸው ነጥቦች መካከል👇 👉“እንዴት አባታቸው ዝም ብለው መሳሪያ ያወርዳሉ” (ልዩ ሃይሉን ነው) 👉“We need money፣ ባለፈው ከሰጣችሁን ገንዘብ አሁን በጣም ያስፈልገናል” ዶ/ር ወንድወሰን ❌ እነዚህ ሰዎች ለህዝብ አይደለም የሚሰሩት ስንል በምክንያት ነው! እራሳችሁ አዳምጣችሁ ፍርዱን ስጡ!
Natnael Mekonnen119,269 views • 3 years ago

ሀብት ከድንቁርና ጋር ሁለት ከባድ ገዳይ ነገሮች ይሄ አርሲ ኔጌሌ ከተማ ውስጥ ነው አሉ። (ሌላ ቦታም ከሆነ ጠቁሙን) አርሲ ነጌሌም ከሆነም የኔጌሌ ከተማ አስተዳደር እና ፖሊስ የለም አልያም በቁሙ ሞቷል ወይንም በይፋ እንዲህ እንዲሆኑ ፈቅዷል ማለት ነው:: ከተማ አስተዳደሩ ይህን ድርጊት በዝምታ ካልፈው ነገ መትረየስ ይዘውለት ይመጣሉ!! አርሲ ነጌሌ ነው የተባለው የሰርገኞቹ ሚዜዎች ጦርሜዳ እንደሚሄድ ሰው ህዝብ መሀል ሰላም ከተማ ውስጥ ሽጉጥ እየተኮሱ ያልፋሉ። እንዲህ አይነት ተራና ህገወጥ ተግባራት ሰላማዊውን ነዋሪ የሚያሸብሩ ብቻ ሳይሆኑ እልም ያሉ የማንአለብኝነትና የብልግና ተግባራት ስለሆኑ ህግ አስከባሪ አካላት እነዚህን ዱርዬዎች በቁጥጥር ስር አውላችሁ ህግና ስርአትን ልታስከብሩ የሚገባ ይመስለኛል። ከቅርብ ግዜ ወዲህ እየተለመዱ የመጡ መስመር የለቀቁ የሰርግ ስነስርአቶች እየታዘብን ነው። ሃብታሞች በ V8 ደሃ ህዝብ ላይ መጨማለቅ አንዳች የሚጨምርላችሁ ክብር የለም። መጨማለቁ አልበቃ ብሏችሁ ደግሞ ሰው ሰላም ወጥቶ እንዳይገባ መሃል ከተማ ላይ የጥይት እሩምታ ታሰማላችሁ። ለሚያያችሁ ሰው ለዚህ እኩይ ድርጊታችሁ መንግስታዊ ፍቃድ ያላችሁ ነው የሚመስለው። በምስኪን ህዝብ መሃል ተከባችሁ እየኖራችሁ በዚህ ልክ መቅበጥ ነውረኝነት እንደሆነ አውቃችሁ ጥጋባችሁን በልክ እንድታደርጉት እንጠይቃለን።
Natnael Mekonnen28,650 views • 7 months ago

ጠቅላይ ሚኒስትሩ Abiy Ahmed Ali 🇪🇹 ትናንት ማታ እንግዳ ተቀብለው ዛሬ ጠኋት ቄለም ወለጋ በመታየታቸው ብዙ ሰዎች ሲገረሙ ታዝቢያለሁ እስከማውቀው ድረስ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትንሹ በቀን ለ 16 እና 18 ሰአታት ይሰራሉ። ይህ በየቀኑ ነው አንዳንዴ እስከ 20 ሰአታት በስራ ላይ ናቸው:: ይሄንን አብረዋቸው የሰሩ ሁሉ የሚመሰክሩት ሃቅ ነው። (አቶ ገዱ ራሱ ቢጠየቁ ለማህተባቸው ይመሰክራሉ 😁) የኢትዮጵያ መከላከያ አመራሮችም በተለይ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላና ጀነራል አበባው ታደሠ ሌሎችም ጀነራሎች ክብርት ከንቲባዋን Adanech Abiebie ጨሮም ቀንና ለሊት እንደሚሰሩ አውቃለሁ። ገና አላሁ አክበር ሳይል ለሊት 10:30 ቢሮ ገብቶ ከለሊቱ ሰባት ሰአት ከቢሮ መውጣት በሰዎቹ ቤት ባህል እንደሆነ ባለችኝ አነስተኛ እድል ለመታዘብ ችያለው። በተለይ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ለመስራት በሳቸው የፍጥነት ልክ መሮጥ ብቻ ሳይሆን አንድ የመንግስት ሰራተኛ ከሚሰራው ሰአት ቢያንስ ሁለት እጥፍ ለመስራት ዝግጁ መሆን አለብህ። ይህንን ከሳቸው ጋር አብረው የሰሩ ቢያንስ አምስት ሰዎች ነግረውኛል። አንዳንዴ አብረዋቸው የሚሰሩ ሰዎች ቢሮ ለሰአታት ሲሰሩ አይተዋቸው እነሱ ቤታቸው ሄደው ቴሌቭዥን ሲከፍቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩን አንዱ ሐገር ሄደው የሆነ ፕሮጀክት ሲመርቁ አይተዋቸው ይገረማሉ። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የስራ ባህልና ጥብቅ Discipline አንዳንዴ ለሚሰማው ሰው ግነት ይመስላል። አብረዋቸው የሚሰሩት ግን ቀን በቀን የሚመለከቱት ጉዳይ ነው።
Natnael Mekonnen17,855 views • 4 months ago

በአዲስ አበባ በዝምታ እየተሰሩ ያለው ምርጥ 5 ሜጋ ፕሮጀክቶች Good Night #Ethiopiaዬ
Natnael Mekonnen12,168 views • 2 months ago

አቶ አብነት በስልክ ሼህ አላሙዲን ጨምሮ የተለያዩ አካላትን በሚያሳፍር መልኩ የሚያማበትና የሚሳደብበትን የስልክ ቅጂ ባለፈው እንደማመጣ ቃል ገብቼ ነበር። እነሆ አድምጣችሁ ፍረዱ። አብነት የሚባለው ሠው ምን ያህል ውለታ ቢስና ባለጌ መሆኑን ከአፉ ከሚወጡት ፀያፍ ቃላት መረዳት ቀላል ነው። እላይ ሲጠብቁት ተንከባሎ ስድብና ሃሜት መንደር የተገኘው አቶ አብነት ገንዘብ እየከፈለ የሼህ አላሙዲንና የአቶ ጀማልን ስም ከማስጠፋት ባለፈ በራሱም አንደበት በዚህ መልኩ የሰዎችን ክብር ሲገረስስና ሲያናንቅ ነው የሚውለው። ያሳፍራል!
Natnael Mekonnen14,666 views • 3 months ago

የጠቅላይ ሚኒስትሩ እውነት ወጣ! የዶክተር አብይ እውነት ሳይውል ሳያድር ወጣ! አቶ ገዱ አብይም እኮ ለክሩ ሲል ይመስክር ያለው ይህንኑ ነው። ለምን ነበር ታዲያ ዋሸ ያሉን? ይኸው ከርስዎ አፍ ቃል በቃል ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ለኢሳያስ ንገሩት ብሎ የላክዎት መልእክት «የሰብአዊ ጥቃት አይፈፀም፣ ሰራዊቱ በግዴለሽነት የሚፈፅመው ጥቃት ይቁም፣ በህዝቡ ላይ የሚደርሱ የሰብአዊ መብት ረገጣዎች ይቁሙ፣ ወታደሩም ጥንቃቄ ያድርግ አስፈላጊውም እርምት ይወሰድ» ነው ብለዋል። አቶ ገዱ ይሄ ማለትኮ በዲፕሎማሲያዊ ቋንቋ “ህዝቤን አትንኩ ፣ንፁሀንን አትግደሉ» ማለት ነው። ይሄ ማለትኮ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ የኤርትራ ሰራዊት የፈፀማቸውን ኢ ሰብአዊ ድርጊቶች ይቃወማል ብቻ ሳይሆን ለማስቆም ልኡካን እስከመላክ ደርሷል ማለት ነው። ይሄ ማለትኮ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፓርላማ ላይ ቀርቦ የተናገረው ሃቅ ነበር ማለት ነው። ምኑን ነበረ ታዲያ አብይ ዋሸ ያሉን? ጠቅላይ ሚኒስትሩ እውነት ከኛ ጋር ነች ብሎ ነበር። ይኸው እውነቱ ከጠላቱ አፍ ሳይቀር እንደውሃ መፍሰስ ጀመረ። አቶ ገዱ መጀመሪያ ቢያንገራግሩም እንዲህ ሃቁን ስላወጡልን እናመሰግናለን። ደግሞ ይሄንንም እንዲያስተባብሉ አዋክበው ሌላ ሚዲያ ላይ እንዳያቀርብዎት እንጂ ላሁኑ ምስክርነትዎ እናመሰግናለን!
Natnael Mekonnen17,816 views • 4 months ago

ባህላዊ ጀነራል የሆነው ምግበይ ሃይሌ በትግራና በአዲስ አበባ እንዲሁ በዱባይ ቤትም ህንጻም የለኝ በማለት ከዘጠኝ ወር በፊት ለኢትዮ ፎረም ጋዜጠኞች የእምነት ክህደቱን ቃል ሰጥቶ ነበር የዛሬ ሳምንት ደግሞ በዱባይም አዲስ አበባም መቀሌም ህዝፃዎችና ቤቶች እንዳሉት ተናግሯል:: ባህላዊው ጀነራል ምግበይ ከብዙ ህንፃዎቹ አንዱ የሆነው በመቖለ ዓዲሽምድሑን የሚገኝ ህንጻው ይሄ ነው:: የአዲስ አበባውን እና የዱባዩን ቤቶችና ህንጻዎቹን በምስልና ቪዲዮ ይዤ እመለሳለሁ:: ይህን ህንጻ ህይወታቸውን የሰው ልጆቻቸውን በግዳጅ የሰጡ ታጋይና የታጋይ ቤተሰቦች መውረስ አለባቸው!
Natnael Mekonnen14,593 views • 3 months ago

የኛ ሰው በሱዳን 😁 ዘሜ ሱዳን ሆኖ መመለሻው መንገድ ጠፍቷታል ስላችሁ ውሸት መስሏችሁ ነበር። ይኸው ከሱዳን ሰላም እያላችሁ ነው። በአለም ታሪክ ጎረቤት ሐገር ተቀምጦ በርቀት የአማፂ ጦርን የሚመራ ታጋይ ዘመነ ካሴ ብቻ ነው 😁 ዘሜ ነፍሱን እንደሚወድ ማንም ነፍሱን አይወድም። አምና ለረመዳን ፆም ነጭ ጀለቢያ ለብሶ ፎቶ ከለቀቀ ወዲህ ዘሜ የኢትዮጵያን አፈር ረግጦ አያውቅም። እንደሲራራ ነጋዴ ጫቱን እየቃመ ከሱዳን ኤርትራ፣ ከኤርትራ ሱዳን ተደብቆ ሲሽሎኮሎክ ነው የኖረው። እሱ ከወያኔና ሻቢያ መመሪያ እየተቀበለ ትግሉን በሪሞት ኮንትሮል ይመራል እዚህ ምስኪን የገበሬ ልጅ ለሱ የማይሳካ የስልጣን ምኞት በየቀኑ ይረግፋል። ደሞኮ ጠቆር ቢል እነሱን ነው የሚመስለው 😁
Natnael Mekonnen18,095 views • 4 months ago

ህወሓቶች ለትግራይ ህዝብ አንድም የልማት ተቋምና ህይወቱን የሚለውጥበ ነገር ሳይሰሩ በቤተሰብ ተደራጅተው ኢትዮጵያን ረግጠው ሲገዙ እና ሲዘርፋ የሕወሐት ደጋፊና ተቆርቋሪ የነበሩ ዛሬ የሕወሐት ባህሪ ተገለጠልን እያሉ ነው ወይ ጊዜ ለትግራይ ወጣቶች እልቂት ከተጠቃሚዎች አንዱ ዳንኤል ብርሃነ ነው:: የሰሜኑ ጦርነት ከመጀመሩ በፊት ጦርነቱን በአስቸኳይ መጀመር አለብን በማለት የህወሓት ሰዎችን በዚሁ ሚዲያ ከዝችው ጋዜጠኛ ጋር ሲያስጠነቅቅ ነበር:: በዳንኤል ብርሃነ ጉዳይ ላለፉት 13 እና 14 አመታት በተከታታይ ጽፌበታለሁ ፈላጭ ቆራጭ በነበረበት ወቅት ዛሬ ይህን ኢንተርቪው ስሰማው ወደኃላ በመመለስ ዳንኤል ለህወሓቶች ምን ያደርግ እንደነበር እያሰብኩኝ ደነቀኝ!
Natnael Mekonnen11,388 views • 2 months ago

“አገዛዙ ደንግጧል” የሚለው ሰውዬ ያስቀኛል ሰሞኑን ኮሜዲያን ያሲኖ “እየሞከርኩኝ ነው” የሚል ድንቅ ድራማ ሰራ። ይሄን ተከትሎ አንድ የክሪስማስ ተርኪ የመሰለ ጋዜጠኛ ነኝ ባይ በማግስቱ አንከር ነው ታንከር በሚል ሚዲያ መጥቶ ድምፁን ጎርነን በማድረግ “በኮሜዶያን ያሲኖ የተጀመረው እየሞከርኩኝ ነው የሚለው ትግል በመላ ሐገሪቱ እየተቀጣጠለ ነው። አገዛዙም በጣም ደንግጧል” ብሎ ዜና ሰራ።😂 ኮሜዲያን ያሲኖ በማግስቱ መጥቶ ይሄን የክሪስማስ ተርኪ የመሰለ ጋዜጠኛ “እኔ ፖለቲካ አላወራሁም እዛው የለመድክበት ሄደህ ተበጥረቅ” ብሎ ኩም አደረገው። ነገር ግን ሀፍረት ባለፈበት ያላለፈው ጋዜጠኛ ነኝ ባይ ሰው “ኮሜዲያን ያሲኖ ያወራኸው ፖለቲካ ነው ብያለው ፖለቲካ ነው” ብሎ ድርቅ አለ 😂 ይሄ “አገዛዙ ደነገጠ” በማለት የሚታወቀው ሰው ሰሞኑን በሐገረ አሜሪካ ቤት ገዝቶ በላቡ ሰርቶ እንደገዛ ሰው ሰንጋ ጥሎ ማስመረቁን ሰማሁ። ድግሱን የታደሙ ወዳጆቼ ከድግሱ እንደወጡ ደውለው ሲያስቁኝ አመሹ። “አስር ግዜ እየመጣ የቤቱን ዋጋ አጋንኖ እየተናገረ አላስበላ አላስጠጣ አለን” ሲሉኝ በሳቅ ልሞት። ይህ ሰው እንግዲህ በሐገሩ ላይ ይህን ሁሉ ጥላቻና ክህደት የፈፀመው ለዚችው ጥሏት ለሚሄደው የአሜሪካ ቤቱ ነበር። ለዚችው ነበር ይህ ሁሉ ክፋትና ተንኮል! በርግጥ ከ15 አመት በላይ አሜሪካ ተቀምጦ ከኡበር ውጪ አንድ ስራ ሳይሰራ የፈረደባት የኢትዮጵያን ፖለቲካ እየተነተነና ህፃናትን ወደጦርነት እንዲገቡ እየሰበከ የገዛ ልጆቹን አስተምሯል፣ አገዛዙ ደነገጠ እያለ የሱንና የቤተሰቡን ሆድ ሞልቷል፣ ትናንት የትግራይ ህዝብ ላይ ዛሬ ደግሞ የኦሮሞ ህዝብ ላይ ጥላቻን እየሰበከ ኑሮውን አደላድሏል። አመፅን፣ ውጊያን፣ ሞትን፣ እያበረታታ ኑሮውን ደጉሟል። ሃሰትንና ቅጥፈትን እውነት አስመስሎ እያቀረበ ለአመታት የኢትዮጵያውያንን ማህበራዊ መሰረት አፈራርሷል። ይህ ጎምበስ ካለ ግማሽ ፍየል ሳይጨርስ የማይነሳው እንደራሱ ታንከር ሚዲያ አለኝ የሚል ሰው ነው እንግዲህ ኮሜድያን ያሲን ያላሰበውን አመፅ ሊያደርግ ነው ብሎ ውጪ ሐገር ተቀምጦ ልጁን የማያውቀው ጉድ ውስጥ ሊከተው የሞከረው። ይሄንን ሰው እኔ የማውቀውን ያህል ሌሎች የሚያውቁት አይመስለኝም። ብዙ ግዜ ትንሽ ኢትዮጵያ ተቀምጠው ስለሐገራቸው የሚያወሩ ሰዎች ብቅ ሲሉ ንግግራቸውን ፖለቲካዊ መልክ ሰጥቶ ዜና ይሰራባቸዋል። አላማው ሰዎቹ እንዲታሰሩና ነገሩ የበለጠ እንዲቀጣጠል እሱም ለዩቲዩብ የሚሆነውን ዜና መቃረም ነው። አስቡት ኮሜዲያን ያሲን የጥበብ ሰውና ትጉህ ሰራተኛ ወጣት ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የህግ አካል አሰሱም ገሰሱም ተናገረ ብሎ አይደነብርም እንጂ እንደ ታንከር ሚዲያ ባለቤቱ የቅጥፈት ፕሮፖጋንዳና ጭካኔ ቢሆን ኮሜድያን ያሲን አመፅ ቀሰቀስክ በሚል በህግ ቁጥጥር ስር በዋለ ነበር። ደግነቱ ያሲኖም ቶሎ ወጥቶ በቂ መልስ ሰጠው። ኮሜዲያን ያሲን ያወራው የሁላችንንም እውነታ ነው። ሁላችን ሃብታም ሆንን ደሃ፣ ትልቅ ሆንን ትንሽ የምንፈልገውን ነገር ለማግኘት እየሞከርን ነው። ኢትዮጵያ እንኳን እንደሐገር ታሪካዊ ግዛቷን ለማስመለስ እየሞከረች ነው። ሌላው ቀርቶ የታንከር ሚዲያ አዘጋጁ ራሱ ሰውየው ዩቱዩቡ ብዙ እንዲታይለት እየሞከረ ነው። :D ሁሉ ሰው ሞካሪ ነው። ሙከራ የስኬት ጅማሮ ነው ብሏል ራሱ ያሲኖ! ይህ ጋዜጠኛ ነኝ ባይ ግን ምንም የማያውቀውን ልጅ ለዩቱዩብ ዜና ብሎ የመስዋእት በግ ሊያደርገው የሞከረበት መንገድ የሰውየውን የልብ ጥቁረትና ትንሽነት በግልፅ ያሳየ ሆኖ አልፏል። comedian_yasino
Natnael Mekonnen14,212 views • 4 months ago