
Neamin Zeleke
@NeaminZeleke • 253,558 subscribers
Lifelong learner & passionate #SocialJustice #Sustainablity #Resilience #ClimateAction #EnergyTransition #SDGs #equity #justice #inclusion #PublicPolicy 🌍
Shorts
Videos

''ውሸቱ የሚቆመው የአብይ አህመድ መንግስት ሲወድቅ ነው። መንግስታት ይዋሻሉ። የአብይ አህመድ ግን በሽታ ነው'' ዶ/ር ዮናስ ብሩ Yonas Biru ሚዲያ Mesay Mekonnen የሰጠው ቃለ ምልልስ። ሰሞንኑን ህዝብ በሙሉ እንደታዘበው "በቁስል ላይ እንጨት ስደድበት" እንዲሉ #ብርቱካን ተመስገን ላይ እያደረሱ ያሉት የበደል በደል የብልጽግና መለያ ምግባሩና ማንነቱ ነው። ከቀደሙት አገዛዞች ሁሉ በተለየ የኦሮሚያ ብልጽግና የሚዘውረው አገዛዝ በተለይም ከመሪው አረመኔ የበሻሻ ደላላ #አብይአህመድ ጀመሮ እስከታችኛው እርከን የነጭ ውሸት ፣ የማጭበርበር፣ የውንብድና ክምር ነው ። አረመኔያዊ ተግባራት ፣ ሸፍጥ፣ ሴራ፣ ነውር፡ ክህደት ፣ ድንቁርና የሚሉ ቃላት ምንነቱን ምግባሩን ሙሉ በሙሉ አይገልጹቱም፣ ከዝቅጠቶቹ ፣ ከስራአትጁ ሞራል አልባነት ፣ ከወራዳነቱ ለ1000 ሺ መገለጫዎች እንዱ ብቻ ነው። ዶ/ር ዮናስ ብሩ የአገዛዙ ቁንጮና የውሸትና የአረመኔነት ክምር የሆነው አብይ አህመድ አይን ያወጣ ተደጋጋሚና አሳፋሪ ውሸቶች ዙሪያ ለአንከር ሚዲያ የሰጠውን ቃል ምልልስ ተከታተሉት፣ የፓርላማ ውሎው ላይ አይኑን ሳያሽ የተናገረቸውን ውሸቶች በዝርዝር ይሄድበታል። ሙሉውን እዚህ ታገኙታላችሁ።
Neamin Zeleke161,868 просмотров • 1 год назад

#AmharaGenocide, #AbiyAhmedAli, the maniacal prince of chaos, having met massive resistance to his unjust war in #Amhara region and deeply frustrated due to his army's demoralized state of affairs, in disarray, is now resorting to igniting a civil war and possible #Genocide in #Ethiopia. The fierce urgency of an impending catastrophe demands that all #Ethiopians inside and abroad urgently come in unison and put on notice the #IC #US #EU #AU, etc. The video is a loud and clear signal for an impending #AmharaGenocide. in #Ethiopia. U.S. Embassy Addis EU Delegation to AU European Commission Mike Hammer Ana Gomes
Neamin Zeleke74,828 просмотров • 2 лет назад

ዛሬ በጠዋት ከ #አዲስአበባ ለረጅም ግዜ የማውቀው ሌላ ወዳጄ ደውሎ በአይኑ ያየውን፣ ወደ አካባቢው ሄዶ ያየውን ጆሮ ጭው የሚያደርግ፣ እንጀት የሚያኮማትር ጉዳይ ነገረኝ። #AbiyAhmed እና የኦሮሞ ብልጽግና የሚባለው የማህብረሰብ ዝቃጮች ጥርቃሞ በአዲስ አባባ ህዝብ ላይ የሚፈጽሙት የነውር፣ የኢ-ፍትሃዊነት፣ የአረመኔነት ጥግ ተግባራት መካከል እንዱን ብቻ የሚመለከት ነው ። ባለፉት ሁለት ቀናት በቦሌ “ፒኮክ መናፈሻ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የነበሩ ቤቶችን በሙሉ አፈረሱ፣ እንድ አዛውንት ራሳቸውን አጥፍተዋል፣ ሌላ ሰው ተገድሎአል፣ ፌደራል ፓሊስና የአዲስ አበባ ፓሊስ አካባቢውን በመውረር በርካታ ዜጎችን ደብድበዋል" አለኝ ። "ማነው ይህን ያስፈጸምው ብዬ ለጠየኩት ጥያቄ ፣ “ጥላሁን የሚባለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር” ተብየው በማለት መለሰልኝ። “በአንድ ሳምት ውስጥ አካባቢውን ልቀቁ ተባሉ” ይህን ኢፍትሃዊ፣ ኢ-ህገ መንግስታዊ ውሳኔ "አቤት ለማለት ደርሰው ሲመለሱ ቤታቸው ፈርሶ ነው ያገኙት"። "ቦታው 200, 000 ካሬ የሚሆን እርሻ ነበር፣ እታክልትና ፍራፍሬ አምራች ቦታ፣ ሙሉ በሙሉ ጉራጌዎች ናቸው 61 ቤተሰቦች እንዳንዶቹ ከ 50 አመት በላይ በአካባቢው ሰፍረው አልምተው ፣ መተዳደሪያ ያደረጉ፣ ካርታና የስራ ፈቃድ ያላቸው ናቸው" ብሎ ነገኝ። "ዚጎችን አናፈናቅልም በማለት "ሌላም ሌላም ብሎ ድፍን የኢትዮጵያን ህዝብ የደለለው አረመኔው የበሻሻ ወሮበላ #አብይአሀድ “የኮሪዶ ልማት” ሊላው ገጽታ የሚያሳዩ መሰል ዘግናኝ አረመኔያዊ ድርጊቶች ሞልተው ፈሰዋል። በዜጎች ላይ የሚፈጨመው የማያባራ አረመኔያዊነት ስላቅና ቧልት፣ ይህ ብልጽግና የሚባል ወያኔ ጠፍጥፎ የፈጠራቸው የማህበረስብ ዝቃጮች አራዊትነት እንደቀጠለ ነው። አላባራም ። በራሱ ተረት ተረትና ሃስት የሰከረው ፋሽታዊው #አብይ አህመድ ነጋ ጠባ የኮሪዶር ልማት በሚል አዲስ አበባን ለአረቦች ለመሸጥ፣ የኦሮሚያ ብልጽግና እና ክሮኒዎቹ፣ በድለላ ሀብት እንዲያካብቱ ማደበልብ ፣ በድሃ፣ አቅመ ደካማ በመቶ ሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ዞጎች የደም እምባ፣ የሚያፈሱበት፣ በርክታቶች ራሳቸውን ያጠፉበት፣ የብልጽግናው ቅጥፈት፣ እብደት፣ ክህደትና ሴራ የወለደው የአምስት ዓመታት የፊዳና የመዓት ኑሮ በኢትዮጲያ! የብልጽግና ፓርቲ ኢትዮጲያን እያፈረሰ፣ ኢትዮጲያዊያንን ያጫረሰ፣ የኢትዮጲያን ስም ያስረከሰ፣ ሀገሪቱን ለኤምሬቶችና የራሱን ህልምና ቅዠት ስልጣን ለሚያራዝሙት ሆዳም ካድሬዎች የሸጠ፣ ደሃን የበደለ ፍትሕን ያጎዳለ አረመኔያዊ አገዛዝ ነው። ======================= ይህን አይን ያወጣ፣ ጥርስ ያገጠጠ አረመኔነት አንድ ጠበቃ ዛሬ ያስነበበውን እናንተም እንብቡት። Andualem Buketo Geda ይሄን ለጥፏል። ቅስም ይሰብራል! አርብ እለት ፒኮክ መናፈሻ አካባቢ አትክልት በማምረት ስራ የሚተዳደሩ ቤተሰቦች እና ልጆቻቸው ቢሮዬ መጡ።'ሰፈሩ ለልማት ሊነሳ ነው እየተባለ ነው።ከወላጆቻችን ዘመን ጀምሮ በአካባቢው ለ73 አመታት ቆይተናል።ድንገት ተነሱ ብንባል ምን ይዋጠን!?' አሉኝ። 'መጀመሪያ የምትሄዱበትን ቦታ ማመቻቸት የመንግስት ግዴታ ነው።ያ ሳይሆን ለማስነሳት እንቅስቃሴ የሚደረግ ቢሆን ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቅርቤ እግድ እንዲሰጣችሁ አደርጋለሁ!' ብያቸው ተለያየን።ቅዳሜ ጉዳዩ የሚታይበትን አግባብ ሳዘጋጅ ዋልኩ።እሁድ ጠዋት ደወሉልኝ ።ከቤተክርስትያን ስንመለስ ቤታችን እየፈረሰ አገኘነው አሉ። ከባልደረባዬ ጋር ሄድን ።አይዟችሁ ብለን መትረፍ የሚችለውን ለማስቆም እንሞክራለን አልናቸው ።እስከ ማታ ለሰብአዊ መብት ኮሚሽን ጨምሮ ለሚመለከታቸው አካላት የህግ አቤቱታዎችን ስናዘጋጅ አመሸን።ሰኞ ጠዋት ኮሚኒቲው ህጋዊ የህብረት ስራ ማህበር ያላቸው በመሆኑ በማህበራቸው ስም ሊቀመንበሩ አቶ ዱላ ኑርጋ ውክልና እንዲሰጡን ተነጋገርን።ትላንት ከሰአት ሊቀመንበሩ የጠበቃ ውክልና ለመስጠት የማህበሩን የመመስረቻ ጽሁፍ ስላጡት ለማክሰኞ ጠዋት እንደሚሰጡን ተነጋገርን ።ዛሬ ጠዋት አቶ ዱላ ከቤታቸው ሲወጡ የማህበሩ አባላት ሰፈር ውስጥ ለማፍረሻ የመጣ ዶዘር ቆሟል።ሌሎች አባላቶች ለኛ ውክልና ለመስጠት ውልና ማስረጃ እየጠበቋቸው ነው።አብራቸው ከቤት የወጡትን ባለቤታቸውን ' መጣሁ እየሄድሽ ጠብቂኝ !' ብለዋት ወደ ቤት ተመለሱ።በአንዲት ቀጭን ሲባጎ እራሳቸውን አንጠልጥለው ተገኘ። ዛሬ ጠዋት 3:00 ላይ እኔ አቤቱታዬን ይዤ የአቶ ዱላን ስልክ ስጠብቅ ከሌሎች አባላቶች ተደወለልኝ።ከዛ ወዲህ ያለው ቢነገርም ጥቅም የለውም። ሰፈሩ መፍረሱ እና መልሶ መልማቱ ላይ ተቃውሞ የሌለውን ኮሚኒቲ በ2 እና በ3 ሰአት እያዋከቡ ማስወጣት መውደቂያውን ሳያውቅ ማሳቀቅ መጨረሻው ይሄ ነው። አቶ ዱላ ለ20 አመት በሊቀመንበርነት ያገለገሉትን ከ70 አመት በላይ በአንድ ቦታ የቆየውን ለፍቶ አዳሪ ማህበረሰብ 'ፌይል አደርጌያቸዋለሁ' ብለው እራሳቸውን አጥፍተዋል።እኔም ያንን ኮሚኒቲ ፌይል አድርጌዋለሁ።ትላንት አቤቱታውን ባስገባ ምናልባት ሊቀመንበሩ ከውሳኔው ይቆጠብ ይሆን?!ከጠዋት ጀምሮ በሰቀቀን ውስጥ ነኝ! ቀብራቸው ነገ ይፈጸማል! ነብሳቸውን ፈጣሪ ይቀበላት !!
Neamin Zeleke43,184 просмотров • 1 год назад
Sensitive content
This media may contain sensitive content.

መደመጥ ያለበት ፦ የ ፕ/ር መሃመድ ሃሰን ከመሳይ መኮንን ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ ሃቁን ያስቀምጣል - ከሃዲና፣ ሴረኛው የአረመኔው የበሻሻ ደላላ የ #አብይአህመድ ክህደትና ቅዠት ከየት ወዴት ?፣ እነ ሙላቱ ተሾመ መስል ቀደም ሲል የወያኔ ፣ ዛሬ ደግሞ የአብይ አህመድ ተላላኪዎች ፣ እንዲሁም ጥቃቅናና አነስተኛ ካድሬዎቹ ዛሬ ላይ በየሚዲያውና ሶሻል ሚዲያ ከሚደልቁት የሃሰት ፕሮፖጋንዳ በተቃራኒው ትላንት እውነታው በእርግጥ ምን ነበር? ዛሬስ ላይ ለምን ተለወጠ?.....“ወያኔ ደብረ ብርሃን ደርሶ ነበር ፡ የሚያቆመው ሌላ ሃይል ባይኖር ኖሮ ፣ አዲስ አባባ ገብቶ ነበር ፡ የነበረው የሃይል አስላለፍ ሳቢያ በ #ኤርትራውያን መስዋእትነትና እርዳታ ነው የአብይ አህመድ ስልጣንም ሊቀጥል የቻለው። ራሱ አብይ አህመድ በተደጋጋሚ ፣ የአብይ አህመድ ጀነራሎች እንዲሁ በተደጋጋሚ የተናገሩት የመሰከሩት ጉዳይ ነው" .....
Neamin Zeleke37,770 просмотров • 1 год назад

ሰላም ወገን #ኢትዮጵያውያን እንዲሁም #ኤርትራውያን ወንድሞችና እህቶች ፥ -የ #ቀይባህር ፣ #የአሰብ የ #አብይአህመድ ካድሬዎቹ እያጦዙት ስለሚገኘው እጅግ አደገኛ አውዳሚ ሂደት፡፦ - የኢኮኖሚያዊ ውድመት፣ የመቶ ሺዎች እልቂት፣ የዲፕሎማሲ ውድቀትና መገለል፣ ሌላም ሌላም መዘዞች ሊያስከትል ሰለመቻሉ፣ በ #ኢትዮጵያ እና በ #ኤርትራ ህዝቦች፣ እንዲሁም በቀጠናው ላይ ሊያደርስ የሚችለው ከባድ ምስቅልቅና ውድመት፣ - ኢትዮጵያ በምን መልኩ ዘላቂ ፣ አስተማማኝ፣ የቀጠናው ሀገሮች ስጋት ሳትሆን፣ አለም አቀፍ ህጎች ተከብረው የባህርና የወደብ ጥቅሞች ማግኘት የሚቻልበት ቀጠናዊ ትስስርና ትብብር ዙሪያ ፦ - በእኔና በጃዋር መሃመድ መካከል ስለቆየው ግንኑነት ። በአብይ አህመድ አገዛዝና የኦሮሚያ ብልጽግና "የምስራቅ አፍሪካ የኦሮሞ ኤምፓየር አጀንዳ"/ የኩሽ ኤምፓየር የበላይነት/ሄጅመኒ አጀንዳ ዙሪያ ፣ ጋጠወጥነት፣ ኢፍታዊነት፣ ለብሄራዊ ደህነትና ጥቅም ጠንቅ ፖሊስዎችና ተግባራት ሀገሪቱን ወደ ዘርፈ ብዙ ቀውሶች የከተቱ ኩነቶች ስለመሆናቸው፦ - የአባቴ የኮማንደር ዘለቀ በጋለ ስም ከእኔ ጋር ተያይዞ ከሰሞኑ በብልጽግና ዲጂታል ካድሬዎች ያሰራጩት ስለነበር ከአሰብና ከቀይ ባህር ጋር ወላጅ አባቴ የነበረውን ቁርኝት በሚመልከት ፦ - ቀደም ሲል በህልውና ጦርነቱ በነበረኝ የፊት ለፊት ሰፊ ተሳትፎ በህወሃት ካድሬዎችና በትግራይ አክራሪ ብሄርተኞች የተሰራጹ የሃስት ትርክቶችና ውዥንብሮች በሚመለከት ፣ ዛሬ ላይ ደግሞ ትላንት ሲያወድስኝ የነበሩ የብልጽግ ካድሬዎች የእነሱን ገልብጠው በእኔ ማንነትና በቤተሰቤ ማንነት ዙሪያ "ግማሽ ኤርትራዊ ነው በሚል፣ እንዲሁም ወገንተኛነቱ ለኤርትራ" ነው በሚል ያሰራጩት የሃስት ትርክትና ውዥንብር በሚመለከትም መልስ ሰጥቼአለሁ። - እንዲሁም በእኔ የትግል ታሪክ ዙሪያ ለሃሳብ ገበታ ሞገስ ዘውዱ Moges Teshome , ሰፊ ቃለ ምልልስ እዚህ ይገኛል። Jawar Mohammed Tamagne Beyene Dawit
Neamin Zeleke24,962 просмотров • 10 месяцев назад

ይህ ስሙን መጥራት የማልፈገው ለአንደበቱም ለሆዱም ለከት ያልፈጠረበት የሰው አሳማ ፣ እጅግ አሳፋሪ፣ ወራዳና፣ ቆሻሻ የሆነው ባህሪውና ስብእናው ለአረመኔው ዋና ወሮበላ ከ #አብይእህመድ እምብዛም ልዩነት የሌለው መሆኑ የሚታወቅ ነው። ከአንድ ውሃ እንደሚቀዱ እንዘንጋ። እስስት፣ እባብ፣ እንዲሁም እይጠ መጎጥ ቅልቅል ነገሮች ፡ ከትቢያ አንስቶ ማን እንዳሳደጋቸው፣ ለሁለት፡ ለሶስትም እስርት አመታት የማን ተላላኪ እንደነበሩ ለህዝብ መናገር እንደ ስድብ ይሆናል። ለማንኛውም ይህን የሰው ዝቃጭ ዘሪሁን ተሾመ የሚባል የሬድዋን ሁሴን ተላላኪ ሌላ ተላላኪ ወሮበላ በሚሰጠው መመሪያ በጃዋር መሃመድ Jawar Mohammed ላይ ያቀረበውን የውሽት ክምር ሞገስ ተሾመ በዚህ በምታዩት ምስል ላይ ደርምሶታል/Debunked. በተጨማሪም "አብጤ" የሚል ስያሜ የስጠው የሰላው ብእረኛ #ካሳአንበሳው በፌስ ቡክ ድህረ ገጹ የጻፈውም ይነበብ። ስውየው አይኑን በትልቅ ጨው የታጠበ እንደ ዋና አለቃቸው አይን ቀቅሎ የበላ በመሆኑ የሚገባው አይደለም እንጂ እኔ እሱን ቢሆን በሬን ዘግቼ ንሰሃ እገባ ነበር። ================ ኤርሚያስ (አብጤ) ዋቅጀራ የገጠሩ አማራ ፖለቲካ ውስጥ የነበረውን አክስዮን ከሸጠ (ከተቀማ?) በኋላ ግራ ገብት ብሎታል፣ አቅጣጫው ጠፍቶበታል፣ ግራ መጋባቱ እንዳይነቃበት ይመስላል "ኮምፓስ" የሚል ሚዲያ ከፍቶ እዛና እዚህ አየተላተመ ነው፣ የኬንያና የአሜሪካ የመረጃ ድርጅቶች (በስም ተዘርዝረዋል) በተመሳሳይ ሰአት ስለ ጃዋር መረጃ መቀያየራቸውን፣ መረጃው አንዱ የአሜሪካ የደንነት ሰው ጠረጴዛ ላይ መድረሱ፣ btw የደንነቱ (agent) ስም ተጠቅሷል 😄፣ ደንነቱ ጃዋርን እንደመረመረው፣ ጃዋር የባጥ የቆጡን እንደቀባጠረ፣ ጃዋር ለደንነቱ ሰውዬ የተናገራቸው (interrogation transcript) አብጤ እንዳሉ፣ የጃዋር ስልክና ላፕቶፕ እንደተበረበሩ፣ ከዛም አንድ ኩንታል ማስረጃ እንደተገኝ፣ የተገኙትን ማሰረጃዋች በዝርዝር ያቀርባል፣ ብቻ ብዙ ነገር ሲል ሰማሁት፣ It contains very detailed information እኮ. 😄 አብጤ ደ*ደብ እንደሆነ አውቃለሁ፣ በዚህ ደረጃ ባዶ መሆኑን ለማወቅ ግን የዛሬዋን ቀን መጠበቅ ነበረብኝ፣ የአብጤ ቀደዳ ተራ ውሸት መሆኑን ለመረዳት የአሜሪካ ህግ እንዴት እንደሚሰራ በደምሳሳው ማወቅ በቂ ነው፣ አንድ ሰው በምንም ምክንያት ተጠርጥሮ በደንነት ሰው ምርመራ ሊደረግበት ይችላል፣ ይህ በሆነ መንገድ ሊታወቅ ይችላል፣ ቢበዛ አንድ ሰው በቁጥጥር ስር ውሎ ለምርመራ ተወሰደ የሚል ነገር በሆነ ሊሰማ ትችል የሆናል፣ ከዛ ያለፈ የማወቅ እድል ግን ዜሮ ነው፣ ምክንያቱም ከፍተኛ የደንነት ሰው የሳተፍበት ምረመራ ቀርቶ የአንድ ተራ ፖሊስ የምርመራ ዝርዝር ጉዳይ ሚስጥር (classified) ይሆናል፣ አብጤ የዘረዘራቸውን መረጃዎች ማግኝት የሚችሉት የአሜሪካ ፍትህ ዲፓርትመነት (DOJ)፣ ፍርድቤት ወይም ሴኔት ነው፣ አብጤ ደግሞ ከነዚህ ውስጥ አንዱም አይደለም፣ የአብጤ ቀደዳ ትተን ነገሩን ትንሽ ሰፋ አድርገን እንመልከተው፣ አብጤ አገኝሁት ያለው መረጃ ትክክል ቢሆንስ? መረጃው leaked አድርጎ አግኝቶት ቢሆንሰ? የዛኔ ነገሩ ከባድ ወንጀል (felony) ይሆናል፣ የማይገባውንና ያልተፈቀደለትን መረጃ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ በመያዙ አብጤ ላይ ክስ ይቀርብበታል፣ አሁንም ቢሆን ጃዋር ለልጆቹ አዝኖ ካለተወው መቀመቅ ሊወርድ ይቻላል፣ በዚህወሬ የአንድ ጃዋር ስም ብቻ አልተነሳም፣ የአሜሪካ ህግና ስርዓት ጭቃ ተለቅልቀዋል፣ *** አብጤ የጻፈው ድራማ አይመስለኝም፣ ድፍን አንጎል መሆኑን የሚያውቅ አንድ ሰው የተጫወተበት ይመስለኛል፣
Neamin Zeleke15,095 просмотров • 7 месяцев назад
Sensitive content
This media may contain sensitive content.

ሰላም ወገኖች፥ እሁድ እለት እንድ የቅርብ ወዳጄ ከአዲስ አበባ ደውሎ የነገረኝ፣”…..በየክፍለ ከተማው ህዝቡን ቤት መቀማት፣ ማፈናቀል ቀጥሎአል። ቤቱን ማፍረስ፣ ቦታውን መውስደ ሲፈልጉ መተማመኛ ፈርሙ ይባላል፣ ምትክ ቤት የለም፣ የሚሰጥ የገንዘብ ካሳም የለም፣ ከየሰፈሩ 100 ዚጎች አፈናቅለው፣ 2—3 ስዎች ቤት ሰጠን ብለው በየሚዲያው ህዝብ ያደናግራሉ፣ "የኮንፉውዝና የኮንቪስን ስትራቴጄ…." በሁለት ቀን ውስጥ ቤቱን ያፈርሱበታል..." "..አንድ የቅርብ ዘመዶቼ ቤተሰብ ስርቪስ ያለው፣ ትልቁ ቤት አላቸው። ባልና ሚስት፣ እንዲሁም አራት ልጆች ይኖራሉ፣ ሰርቪሱን አከራይተዋል…..በሁለት ሳምንት ውጡ ተብለዋል። ህዝቡ ደም እምባ እያለቀሰ ነው፣ የእኔ ዘመድ ፣ ደም ብዛት አለባት ፣ ስኳር አለባት፣ ቤታቸው ልጠይቃቸው ስሄድ አመድ መስላለች:: በጣም ደነገጥኩ …” በማለት ዶ/ር መስንበት አሰፋ የጻፈውን በአዲስ አበባ በህዝብ ላይ እየደረሰ የሚገኘውን በደል ፣ የብልጽግና መሪዎችና ካድሬዎች ከስብእና የራቁ አረመኔ ፣ አራዊትነት፡ አጫወተኝ። ተመሳሳይ አሳዝኝ ታሪኮችን ከብዙ አቅጣጫዎች መስማት የተለመደ ሆኖአል። እንዲህ አይነቱን በዜጎች ላይ የሚፈጸም ደበል ፣ የግፍ ግፍ በሺዎች አባዙት፣ ሌላው እንደዚህ አይነት ጋጠ ወጥ፣ ሀገ ወጥ፣ ኢ-ፍትሃዊ ተግባር መንግስትም ሆነ ማንም አካል እንዳይፈጽም መንግስት ቦታ ክፈለገ ካሳ ከፍሎ፣ በቂ ግዜ ሰጥቶ መሆን አለበት የሚለውን ህግ አግድው፣ ለአረመኔ ፣ ኢፍትሃዊ፣ ኢ-ህገ መንግስታዊ ፣ ተግባራቸው እንዲመች አድረገው ነው አየፈጸሙ የሚገኙት። ‘እኛ እናፈናቅልም፣ አንገልም፣ ሳናጣራ አናስርም” በማለት የኢትዮጵያን ህዝብ የደለለው አረመኔው የበሻሻው ወሮበላ “የኮሪዶር ልማት” በመቶ ሺዎች ኢትዮጵያውያን ዜጎች ደም፣ እንባ፣ ህይወትና በቁም መቀበር ላይ መሆኑን ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ማወቅ አለባቸው። ከቤት ማፍረስ ጋር በተያያዘ 60 ሰዎች ራሳቸውን አጥፍተዋል፥ መፈንቀለ መንግስት በትግራይ እንከር ሚዲያ የዘገበውን ተከታተሉት ።
Neamin Zeleke27,063 просмотров • 1 год назад

#አዲስአበባ ወጣቷ በምድረ ኢትዮጵያ ያፈጠጥፈውን ፣ ያገጠጠውን ሃቅ ትናገራለች ። "ረሃብ አይለመድም " ። የጤና በለሞያዎች ረሃብም እንዲሁ። የሞያ ፍቅርና ስነ ምግባር እንጂ የሞያ ፍቃድ አይደለም የራባቸውን ሃኪሞች እና የጤና ባለሞያዎች ስራ ላይ ያቆያቸው። --የአዲስ አበባ ህዝብ የአረመኔው #አብይአህመድን የኮሪዶር ብልጭልጭን ለምዶታል፣ "ረሃብ ግን አይለመድም" -- "የቦሌ መንገድ አበቦች ከ 11 ሰአት ጀምሮ በቂ በላይ ውሃ ይጠጣሉ። የአዲስ አባባ ህዝብ ግን በሳምንት አንድ ቀን ንጹህ ውሃ አያገኝም። ለውሃ ይከፍላል። ለመድነው። "ረሃብ ግን አይለመድም" -- "የአዲስ አበባ ለሊቱን ሁሉ ስታብረቀርቅ ታድራለች፣ ነገር ግን የአዲስ አበባ ህዝብ መብራት አያገኝም ፣ ለመብራት ግን ይከፍላል። ለመድነው...." " ረሃብ አይለመድም" የ
Neamin Zeleke21,145 просмотров • 1 год назад

የአቶ #ታየ ደንድአ ለህዝብ ይፋ ያደረጋቸው የአብይ አህመድ ወንጀሎችና ጉዶች በብልጽግናው መንደር ከፍተኛ ሽብር ፈጥሮአል። አቶ ታየ ደንድአ ማንም የማያደርገውን፣ በእርግጥም ጥቂቶች ብቻ የታደሉትን ወኔና ቆራጥነት የተጎናጸፈ የዘመናችን የፍትህ አርበኛ፣ ጀግና ነው። ልጆቹን ይወዳል፣ ባለቤቱን ይወዳል ፣ ነገር ግን ፍትህ፣ ነጻነትና እኩልነትን በማስቀደም ማንኛውንም አይነት መስዋእትነት ለመቀበል ቆርጦ ፣ ሞትንም አይኑን አፍጦ እያየ እውነትን ተናገረ። የአረመኔውን #አብይአህመድ ጉድ በዝርዝር ለህዝብ አጋለጠ። የአብይ አህመድን አረመኔነት ፣ የአገዛዙን ኢስበአዊነት እያወቀ ፣ ለሞት ሊዳርገው የሚችለውን ነፉሱን አስይዞ አደረገው። ህዝብ ማወቅ ያለበትን ሁሉ ለኢትዮጵያ ህዝብ በመናገር የመርህ ሰው፣ የፍትህ ሰው፣ የእውነት ሰው መሆኑን አስመሰከረ። ከአቶ ታየ ደንደአ ጎን እንቁም።የአቶ ዮሃንስ ቧያለውን፣ የአቶ ክርስትያን ታደለን፣ የመስከረም አበራንየፍት፡ ሌሎችም የፍትህ አርበኞች መስዋእትነት የሚከፍሉበትን የፍትህ፣ የነጻነት አርማ እ ሁላችንም እናንግብ! ከአብይ አህመድ አረመኔ ፋሽስታዊ፣ ጸረ ህዝብ አገዛዝ ጋር የሚደረገውን ትግል ይፋፋም!! የፋኖን ትግል እናጠናክር! በሁልም ዘርፍ የመርዳት፣ የመደገፍ ሃላፊነታችንን እንወጣ! ነጻነት፣ ፍትህ፣ እኩልነት ለኢትዮጵያውያን ሁሉ !
Neamin Zeleke19,455 просмотров • 1 год назад

በ #አማራ ህዝብና በ #ኢትዮጵያ ህዝብ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን የአማራ #ፋኖ ሃይሎች እንድነት ብስራት ማግስት የፋኖ ሰራዊት በዚህ መልክ ደስታቸውን ሲገልጹ የሚያሳይ ምስል። ጥምቀትን ደርበው ሲያከብሩ። የአማራ ፋኖ ብሄራዊ አንድነት ንቅናቄ (የአፋብሃ እና የአፋህድ ውህደት) የአማራን ህዝብ ህልውና፣ መብቶችና ነጻነቶች በማረጋገጥ ፣ ብሎም ሁሉም የኢትዮጵያ ማህበረስቦች መበቶችና ነጻነቶች ለማዋለድ እንድ ትልቅ ታሪካዊ እርምጃ ወስደዋል። ከእንግዲህ የእናቴ መቀነት ጠለፈኝ ማለት እይገባም። በመሬት ላይ የአማራ ህዝብ የሚከፍለውን መስዋእትነት የሚመጥን አለም አቀፍ የዲፕሎማሲ፣ የህዝብ ግንኙነት፣ የሪሶርስ ሞቦላይዜሽን ተግባራዊ በማማደርግ ሁላችንም የድርሻችንን እንወጣ። ድል ለአማራ ህዝብ ! ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !
Neamin Zeleke11,524 просмотров • 6 месяцев назад

A Must Listen: An appeal from Dr. Bruck, a Medical Doctor in #Ethiopia, on their suffering & plight , their just and fair demands, the ongoing repression by #AbiyAhmed's regime, and a call for solidarity from Ethiopians across the Globe and International civil society and human right groups. . #StandInSolidarity #HealthcareHeroes #TeachersMatter #CivilServantsDemandChange #LivingWagesNow #PeopleOverPalace Stand up. Speak out ! . Mobilize your communities ! Protest tirelessly! For freedom. For dignity. For every Ethiopian—no matter their ethnicity or region—whose voice has been stolen. Let our collective roar be heard across the world. The Ethiopian people expect and deserve it
Neamin Zeleke19,680 просмотров • 1 год назад

አረመኔው አብይ አህመድ በአማራ ህዝብ ላይ የከፈተው ሌላ ዙር ሰፊ ጦርነት የዘረኛና ግፈኛ ስርአት አከርካሪ የሚሰበርበት፣ ግበተ መሬቱን የሚያፋጥን ሂደት እንደሚሆን የሚያጠራጥር አይደለም። የተቆጣ፣ የቆረጠና፣ ለህልውናው የሚፋለምን ህዝብ ያሸነፈ ጨቋኝ፣ ግፈኛ ፣ ዘረኛ፣ ጋጠ ወጥ አገዛዝ በታሪክ የለምና!! ደም የማይጠግበው የበሻሻው ቫምፓየር ባለፉት አስራ አራት ወራት የአማራን ህዝብ ለማንበርከክ ስራዊቱን አዝምቶ ያካሄደው የእብሪት ጦርነት የአማራን ምድር በደም ጎርፍ ሲያጥበው ቆይቶአል። በእብሪት በጀመረው ጦርነት የአስርት ሺዎች ኢትዮጵያውያን እይተኬ ህይወት ጠፍቶአል። የአለም አቀፍ ተቋማት ጥናቶች ጭምር ያወጧቸው ዘገባዎች እንደሚያረጋግጡት በከባድ መሳሪያና በድሮ ጥቃቶች በብዙ መቶ የሚቆጠሩ ንጹሃን ዘጎች ተገድለዋል፣ የኢሰመኮ ዘገባ እንደሚያሳየው በአብይ አህመድ ንጹሃን፣ አዛውንት፣ ነፍሰጡሮች፣ ካህናት፣ ያልታጠቁ ገበሬዎች ጨምሮ በአብይ አህመድ ባዘመተው ስራዊት በግፍና በጭካኔያዊ ግድያ ህይወታቸውን ተነጥቀዋል። ውድ ህይወታቸውን በጦርነት ያጡ፣ አካለ ጎደሎ የሆኑ፣ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ የመከላከያ ስራዊቱ አባላትን ይጨምራል። በቢሊዮኖች ዶላር የሚገመት የመሰረተ ልማትና ተቋማት ወድመዋል። ነገር ግን የበሻሻው አረመኔ እርካታ ሊያገኝ አልቻለም። የበሻሻው ንጉሰ ነገስት ስልጣኑ በከፍተኛ ስጋት ውስጥ የጣለውን ፋኖን ካልደመሰሰ፣ ቅዠት የሆነበትን ጀግናውን የአማራ ህዝብ ካልንበረከከ ህልምጁና ቅዠቶቹ ሊያሳኩ እንደማይችል ያውቀዋል። ደም መጣጩ ዛሬም እንደ ትላንቱ የጦር ሃይሉን ከሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች አሰባስቦ "የመጨረሻ ዘመቻ" በሚል እያዘመተ ይገኛል። ክንደ ነበልባሎቹ የአማራ ፋኖ በየአካባቢው በሚገባው ቋንቋ እየተቀበሉት እንደሆነ ልዩ ልዩ የመረጃ ምንጮች ዘግበዋል። ላለፉት አስራ አራት ወራት "እንዴ ህግ ማስከበር" በሌላ ግዜ "በአስቸኳይ ግዜ አዋጅ" ሽፋን ያዘመቱት ሰራዊት በአብዛኛው ሙት፣ ቁስለኛ ሆኖአል። በአስርቱ ሺ የሚቆጠሩ በፋኖዎች ተማርከዋል፣ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ከምድባቸው ጠፍተዋል። ሞራልም አላማም የሌለው ስራዊት ይዞ የተቆጣ፣ የበገነን ህዝብ ለማንበርከክ ፈጽሞ አይቻልም። የበሻሻው ደላላም ሆነ ህወሃት ጠፍጥፎ የሰራቸው ህሊናም አምሮም የተሰለቡ ብልጽግና/የብልግና የልበ ደንዳኖችና ደናቁርት ገዢዎች ጥርቃሞ ይህ ሃቅ የሚገለጽላቸው ፍጡሮች አይደሉም። አብይ አህመድና የአማራ ብልጽግና ተላላኪዎቹ ምንም ያህል ቢንፈራገጡ እንቅሮ የተፋቸውን የአማራ ህዝብ ሊያንበረክኩት ፣ ሊያስገብሩት አይችሉም።
Neamin Zeleke25,503 просмотров • 1 год назад

''ቀጣዩ ተልዕኮ ጦርነቱን ከአማራ ክልል ማውጣት ነው'' ረ/ፕ ጌታ አስራደ - የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ መምሪያ ሃላፊ ለእንከር ሚዲያ የሰጠውን ቃለ ምልልስ በጥሞና ተከታተሉት። የፋሽስቱ የአብይ አህመድ ያዘመተው ወራሪ ስራዊት በአራቱም የአማራ ክልል አካባቢዎች አሁንም በድጋሚ ፣ ለ8ኛ/9ኛ ግዜ ለከባድ ሽንፈቶች፣ የሰብአዊ፣ የቁስና ፣ የሞራል ኪሳራ እየተዳረገ ይገኛል። አሁንም እንደቀደሙት 15 ወራት ሌላ ቀነ ገደብ አስቀምጦ በአራቱም አቅጣጫ እንደ አዲስ የዘመተው ስራዊት እንዳልነበር ሆኖአል። በአለፉት በርካታ ቀናት ብቻ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ የወራሪው ስራዊት ልዩ ልዩ ሬጅመንቶች አባላት ሙት፣ ምርኮና፣ ቁሰለኛ መሆናቸውን በርካታና ከበቂ በላይ የመረጃ ምንጮች ያረጋገጡት ሃቅ ነው። ሸዋ ፋኖ እንዲሁም የጎንደር ፋኖ ለአንከር ሚዲያ ያጋሩትን የእውደ ውጊያ መረጃዎች በጥሞና ተከታተሉት።
Neamin Zeleke24,114 просмотров • 1 год назад

ይሄን ጉድ ተመልከቱ፣ “አፍርሰን ወደ መከላከያ/ፌዴራል ፓሊስ እንዲቀላቀል ተደርጎአል” የተባለለት የኦሮሚያ ልዩ ሃይል ወይንም የነ ሽመልስ አብዲሳ “የመጨረሻው ምሽግ” በምንጃር አውሮ ጎዳና ከተማ አማራ ተወላጅ ንጹሃን ዜጎችን በጭካኔ ከገደሉና ካፈናቀሉ በኋላ ውድመትና ዘረፋቸው ይሄው ! በእኩልነት ስም የበላይነት፣ “በኢትዪጵያ አትፈርስም” ፣ምናምን ሽፋን በደል መፈጸም፣ የመሬት ወረራ ፣ አረመኔያዊ ግድያ፣ ነውረኝነት፣ ጋጠ ወጥነት፣ ህገ ወጥነት ፣ ኢ-ህገ መንግስታዊነት የ #AbiyAhmedAli የሽመልስ እብዲሳ የኦሮሚያ ብልጽግና እይነተኛ መገለጫዎች ይቀጥላሉ። ለዚህም ነው በተባበረ ትግል ይህን ግፈኛ፣ ዘራፊ አገዛዝ መወገድ ያለበት። ድል ለፋኖ ህዝባዊ ሃይል! #FanoCourage #AmharaResistance #WaronAmhara ምስል ከ @ ግዮን አማራ
Neamin Zeleke32,322 просмотров • 2 лет назад

#FanoCourage የአብይ አህመድ መጫወቻ በሆነው የዛሬ ፓርላማ ውሎ የፍትህ ሚንስትሩ ጌድዮን ቲሞትዮስና የፓርላማው የብልጽግና ካድሬዎች ሲደራርቱት የነበረው “ህግና ህገ መንግስት” ማክበር የሚል ነበር። "ህግና ህገ መንግስት" ነገር በአብይ አህመድ አገዛዝ አፈር ድሜ እንደበላ እንድ ከህሊናው ያልተጣላ የዚሁ የጉደኛ የፓርላማ አባል የተናገረው ፍንትው አድርጎ ያሳያል። የራሱን “ህግና ህገ መንግስት” የማያከበር አገዛዝ አምባገናናዊ ፣ፍትሃዊ፣ ሰው በላ በመሆኑ የግዜ ጉዳይ እንጂ በህዝብ ትግል መገርስሱ እይቀሬ ነው። ለጋዜጠኖች ዝግ ተደርጎ የአብይ አህመድን እስቸኳይ ግዜ እዋጅ ለማራዘም በተጠራው የፓርላማ ውሎ ፣ መራራውን ሃቅ ከተናገሩት የፓርላማ አባል ንግግር የተወሰደውና ሾልኮ የወጣው የድምጽ ቅጂ እናዳምጠው። “የዛሬ 6 ወር የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ሲታወጅ ተቃውመናል። - ከዚህ በፊት የጸደቁ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጆች የሰላም እጦትን ከማባባስ ውጪ በጎ ለውጥ አላመጡም። - የሚያስፈልገን መደራደር መነጋገር የሕዝብ ጥያቄን መስማት ነው። - ጥቃቶች እንደሚባባሱ ተናግረናል፤ ንጹሃን ተጨፍጭፈዋል። - ሃሳባቸውን በነጻነት በመግለጻቸው የምክር ቤት አባላት ክርስቲያን ታደለ፣ ዶክተር ካሳሁን፤ ዮሃንስ ቧያለው ታስረዋል። - ሕገመንግስቱ በማይፈቅድበት ሁኔታ በርካቶች ወደ ከርቸሌ ተወርውረዋል። - አቶ ታዬ ደንዳ፤ ዶክተር ደሳለኝ ተደብድበው ወደ ማጎሪያ ካምፕ ተወርውረዋል። - ድንበር ይጠብቃሉ ለክፉ ቀን ይሆናሉ የተባሉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እየሞቱ ነው። - እውነተኛ ንግግር እና ድርድር እስካሁን አልተካሄደም፤ መንግስት በሚዲያዎች የሚናገረው እውነት አይደለም። - አመራሮች እየሞቱ ነው፤ - የመድሃኒት እጥረት ተከስቷል። - በርካታ የልማት ተቋማት እየወደሙ ነው። ( የፓርላማ አባሉ ) - መንግስት እንደ ጎረምሳ ፊት ለፊት ይዋጣልን የሚለውን ነገር አቁሞ ሰከን ብሎ መደራደር አለበጥ ተደብድበዋል ተንገላተዋል። መንግስት ይረጋጋ ። “
Neamin Zeleke28,773 просмотров • 2 лет назад