#fanocourage

NeaminZeleke's profile picture

#FanoCourage የአብይ አህመድ መጫወቻ በሆነው የዛሬ ፓርላማ ውሎ የፍትህ ሚንስትሩ ጌድዮን ቲሞትዮስና የፓርላማው የብልጽግና ካድሬዎች ሲደራርቱት የነበረው “ህግና ህገ መንግስት” ማክበር የሚል ነበር። "ህግና ህገ መንግስት" ነገር በአብይ አህመድ አገዛዝ አፈር ድሜ እንደበላ እንድ ከህሊናው ያልተጣላ የዚሁ የጉደኛ የፓርላማ አባል የተናገረው ፍንትው አድርጎ ያሳያል። የራሱን “ህግና ህገ መንግስት” የማያከበር አገዛዝ አምባገናናዊ ፣ፍትሃዊ፣ ሰው በላ በመሆኑ የግዜ ጉዳይ እንጂ በህዝብ ትግል መገርስሱ እይቀሬ ነው። ለጋዜጠኖች ዝግ ተደርጎ የአብይ አህመድን እስቸኳይ ግዜ እዋጅ ለማራዘም በተጠራው የፓርላማ ውሎ ፣ መራራውን ሃቅ ከተናገሩት የፓርላማ አባል ንግግር የተወሰደውና ሾልኮ የወጣው የድምጽ ቅጂ እናዳምጠው። “የዛሬ 6 ወር የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ሲታወጅ ተቃውመናል። - ከዚህ በፊት የጸደቁ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጆች የሰላም እጦትን ከማባባስ ውጪ በጎ ለውጥ አላመጡም። - የሚያስፈልገን መደራደር መነጋገር የሕዝብ ጥያቄን መስማት ነው። - ጥቃቶች እንደሚባባሱ ተናግረናል፤ ንጹሃን ተጨፍጭፈዋል። - ሃሳባቸውን በነጻነት በመግለጻቸው የምክር ቤት አባላት ክርስቲያን ታደለ፣ ዶክተር ካሳሁን፤ ዮሃንስ ቧያለው ታስረዋል። - ሕገመንግስቱ በማይፈቅድበት ሁኔታ በርካቶች ወደ ከርቸሌ ተወርውረዋል። - አቶ ታዬ ደንዳ፤ ዶክተር ደሳለኝ ተደብድበው ወደ ማጎሪያ ካምፕ ተወርውረዋል። - ድንበር ይጠብቃሉ ለክፉ ቀን ይሆናሉ የተባሉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እየሞቱ ነው። - እውነተኛ ንግግር እና ድርድር እስካሁን አልተካሄደም፤ መንግስት በሚዲያዎች የሚናገረው እውነት አይደለም። - አመራሮች እየሞቱ ነው፤ - የመድሃኒት እጥረት ተከስቷል። - በርካታ የልማት ተቋማት እየወደሙ ነው። ( የፓርላማ አባሉ ) - መንግስት እንደ ጎረምሳ ፊት ለፊት ይዋጣልን የሚለውን ነገር አቁሞ ሰከን ብሎ መደራደር አለበጥ ተደብድበዋል ተንገላተዋል። መንግስት ይረጋጋ ። “

Neamin Zeleke

28,773 Aufrufe • vor 2 Jahren

Keine weiteren Inhalte verfügbar