Загрузка видео...

Не удалось загрузить видео

На главную

ጠሚ አብይ ከ14 አመት በፊት ስለወደብ የተናገሩት

20,276 просмотров • 2 лет назад •via X (Twitter)

Комментарии: 10

Фото профиля ⓉⓃ
ⓉⓃ2 лет назад

Cough up $$ and use the port. There ain't no such thing as a free lunch (TANSTAAFL) ...

Фото профиля Ephraim ኤፍሬም 🙏🇪🇷🦅🇪🇷☕️
Ephraim ኤፍሬም 🙏🇪🇷🦅🇪🇷☕️2 лет назад

So what????? When little baby cry 😭 Assab Assab still . Not any more . If we want we can give to North Korea or Russia to empower their nuclear ☢️ power. Don’t look back Run away from US . ክህደት ምን ዋጋ እንደሚያስከፍልህ ታየዋለህ። ጅቡቲ ወደብ ዋጋ ጭማሪ is on the way .

Фото профиля Samuel Mosazghi
Samuel Mosazghi2 лет назад

''የሞተ ትርክት''

Фото профиля Eyob
Eyob2 лет назад

His chair is already start shaking, it's the matter of time.

Фото профиля EPH I•F A N O 💪🏽💪🏽💪🏽
EPH I•F A N O 💪🏽💪🏽💪🏽2 лет назад

ወደብ ውስጥ ከነ ቤተሰብህ ስመጥ ውሻ

Фото профиля hope
hope2 лет назад

You can bring a footage from the renaissance time if you would like. Asseb belongs to Eritrea. Period !!

Фото профиля Debissa M.M
Debissa M.M2 лет назад

In the making Everything is planned The only difference is the nature of messenger That he even don't know what the next message is He will know after he delivered the current

Фото профиля MaiGiff
MaiGiff2 лет назад

So???

Фото профиля ቦቸፊላ
ቦቸፊላ2 лет назад

ቆይ አሁን ይሄ ድንቅ ነውአህያ? ስለ የወደብ ስርቆት በኢትዮጵያ ታሪክ ማን ያልተናገረ መሪ አለ እስኪ ንገረኝ? ከ100 ዓመታት በላይ ማን ምን ያላለ ደስ የሚለው የኤርትራ ህዝብ ሁሉንም እንደአባባላቸው ወደሚገባቸው ቦታ ሸኝተዋቸዋል,አሁንም ይቀጥላል።

Фото профиля Yonas Tadesse
Yonas Tadesse2 лет назад

አብቹ እሩቅ አሳቢ የክፍለዘመኑ ምርጥ የኢትዮጵያ ድንቅ መሪ ክበርልን!!!!😍😍😍🇪🇹🇪🇹🇪🇹💪💪💪💪🙏🙏🙏🙏🙏

Похожие видео

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ Abiy Ahmed Ali 🇪🇹 ከ20 ዓመታት በፊት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስን ዘመናዊ ተቋም ለላድረግ ምን መሰራት እንዳለበት የተናገሩት ንግግር ነው:: ፌደራል ፖሊስ አሁን ለደረሰበት ብቃትና ዘመናዊነት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የዛሬ 20 አመት ንግግርን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው:: ዝም ተብሎ ብሎ አራት ኪሎ ቤተ መንግስት አልተገባም:: በዕውቀት፣ በትጋት፣ በራዕይ እና በመሪነት ብቃት ነው አራት ኪሎ ቤተ መንግስት የሚገባው። በወቅቱ ከእሳቸው በዕድሜና በልምድ የሚበልጡ የመንግስት ኃላፊዎችን በማስተማር፣ የቴክኖሎጂና የዘመናዊ አስተዳደር እውቀትን በማስረዳት እና ለሀገር ተቋማት ራዕይን በማስጨበጥ ሰርተዋል። በአጭሩ መልዕክቱ የሚለው፦ ስልጣን በወሬ፣ በሐሜት ወይም በጦርነት አይገኝም፤ እውነትን እና ተስፋን ይዞ በመስራት፣ በመማር እና በማስተማር ህዝብን በስራ በተግባር በማሳመን ነው ሀገር የሚመራው እና ትልቅ ኃላፊነት መድረስ የሚቻለው። እነ ጽንዶ ይሰማል? 👂የለም እውቃለሁ 👀 ታውሯል 🫡

Natnael Mekonnen

12,869 просмотров • 2 месяцев назад

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሊጠኑ ይገባል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ Abiy Ahmed Ali 🇪🇹 “በጥቂት አመታት ውስጥ ሮቦቶች በየቤቱ ታያላችሁ” ሲል ዛሬ ግራ የገባቸውም ለማሽሟጠጥ የሞከሩም ሰዎች እያየን ነው። አብይ ከ 17 አመት በፊትም ሐገሬው የስማርት ስልክ ተጠቃሚ ሳይሆን ስለ Mobile Banking አገልግሎት ሲያወራ እንዲሁ ግራ የገባቸው ሰዎች ነበሩ። አንድ መሪ መሪ የሚባለው የዛሬን ችግርና ተግዳሮት ብቻ እየፈታ ሲኖር ሳይሆን ከማህበረሰቡ እየቀደመ የሚያቅድ ህልመኛ (visionary) ሲሆን ጭምር ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩን ከማደንቅበት አንዱ ምክኒያት ህልመኛነቱ ነው። እሱ አንድ ነገር ሲናገር ጠላቶቹ በፍፁም አይሆንም ብለው ይቃወማሉ። የተናገረውን በተግባር አድርጎ ሲያሳያቸው ደግሞ ወደማጣጣል ይገባሉ። እንዲህ ነው ላለፉት አመታት የመጣነው። ከ 7 አመት በፊት ድሮን እንታጠቃለን ብሎ ያሰበ አልነበረም። ከሰባት አመት በኋላ ድሮን ከመታጠቅ አልፈን ድሮን መገጣጠም ጀምረናል። ዛሬስ ከዚያ አልፈን Hypersonic weapons እና ሌሎች ነገሮችን ታጥቀን እንደሆነስ ማን ያውቃል? አብይ በጥቂት እድሜው የብዙ ሰው ህይወት የኖረ ይመስለኛል። በአጭር እድሜ ወታደርም፣ የቴክኖሎጂ ባለሙያም፣ ዶክተርም፣ የፖለቲካ አታጋይም፣ የሐገር መሪም፣ ወዘተ እንዴት መሆን ይቻላል? አንዳንዶች ለሐገር በመታገል ሰበብ ሁለት ፀጉር እስኪያበቅሉ ድረስ ሐገራቸውን ይታገላሉ። አንዳንዶች በሽምግልና ዘመናቸው ለጠላት በመላላክ እድሚያቸውን ይጨርሳሉ። እንደአብይ አይነቱ ከህፃንነቱ ጀምሮ ሐገር ያንፃል፣ ተቋም ይገነባል፣ ድንበር ያሰፋል፣ ትውልድ ያዘምናል። ያለፉ ስብራቶችን ያክማል፣ ያለፉ ስህተቶችን ያርማል፣ የሚያስቀና ህይወት። ሊጠና የሚገባው የህይወት ጉዞ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ሆይ የእርስዎ ትውልድ አካል በመሆኔ ደስታ ይሰማኛል ስል በታላቅ ኩራት ነው።

Natnael Mekonnen

26,334 просмотров • 1 год назад

ታላቁ ቅሌት ሃብታሙ ከሚሰራበት የ 360 ስቱዲዮ እቃ ሰርቆ ሊወጣ ሲል እጅ ከፍንጅ ተይዞ እንዲህ ሲዋረድ ሳይ ለሱ እኔ ተሸማቀቅኩ። ከጋሻ ጃግሬው ገሰር ሊያመልጥ ሲል የያዙት ሰዎች "አንተ በምን ሞራልህ ነው አብይን የምትናገረው" ሲሉም ሰማሁ። ሃቅ ያናግርህ ይላል የወሎ ሰው። እነዚህ ናቸው እንግዴ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ሲሰድቡ የሚውሉት ጎበዝ። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ 49 አመቱ ነው። ሃብታሙ አያሌው 46 አመቱ ነው። ሽመልስ አበራ ጆሮ 59 ወይም ከዚያ በላይ ነው። አብይ 18 አመት ሳይሞላው ወታደር ሆነ። አርባ አመት ሳይሞላው ኮረኔል ሆነ። የሐገሪቱን ትልቅ ተቋም ኢንሳን መሰረተ። PHD ውን ያዘ። በ 42 አመቱ የታላቋ ሐገር ኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነ። በ 43 አመቱ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ግዜ የአለም ትልቁን የሰላም የኖቤል ሽልማት ተሸልሞ ሎሬት ተባለ። ይህ ሁሉ የሆነው ገና 45 አመት ሳይሞላው ነው። ሃብታሙና ሽመልስስ? ዘንድሮም በሐገረ አሜሪካ የካሜራ ሌባ ተብለው በአደባባይ ይዋረዳሉ። 😄አምነው ሃላፊነት የሰጧቸው ጓደኞቻቸውን ክደው እቃ ደብቀው ሊያወጡ ሲሉ በፖሊስ ኪሳቸው ተበርብሮ ይባረራሉ። ከዛ ለተልካሻ ካሜራ ያልታመኑ ሰዎች 130 ሚሊየን ህዝብ የሚያስተዳድረው ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ አንድ ክፍል ተሸሽገው ይበጠረቃሉ። የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ውሳኔውን ላንተ ትተናል። አንዲት ደቃቃ ስቱዲዮ ተስማምተው መምራት ያቃታቸው የገንዘብ አንበጣዎችና የዩቱዩብ ኩብኩባዎችን እየሰማህ የጠላት መጠቀሚያ አትሁን። ቻይኖች ሲናገሩ "ወሬ ሩዝ አይቀቅልም" ይላሉ። የሚያወራልህን ሳይሆን በተግባር የሚሰራልህን ተመልከት። በመዋጮ የተገዛን ካሜራ ሰርቆ የሚያመልጥ ታጋይ ሐገርህን ሽጥልኝ ቢባል አይኑን ሳያሽ "ስንት ብር?" እንደሚል የታወቀ ነው። ከሁሉም ጋር እንተዋወቃለንኮ። እኛ ብንናገር የሚሰማን አጥተን ነበር ይኸው ከጀርባ የሚወጓት የኢትዮጵያ አምላክ በራሱ ግዜ ፀሃይ ላይ አሰጣቸው። አሁንኮ ሃብትሽ አይኑን በጨው አጥቦ ፖለቲካ ሊተነትን ይመጣ ይሆናል። መቼስ ሐፍረት አያውቅም። አይዞሽ ገለቴ አለ ቀነኒሳ 😄

Natnael Mekonnen

16,933 просмотров • 10 месяцев назад

አብይ አህመድ “ይሉሽን በሰማሽ ገበያ ባልወጣሽ” የሚለውን አባባል አያውቀውም መሰለኝ? አብይ አህመድ፣ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስቴር፣ እሮብ እለት ጥቅምት 18 2018 በኢትዮጵያ ተወካዮች ምክር ቤት ውስጥ፣ ለምክር ቤቱ አባላት ጥያቄዎች መልስ በመስጠት ሰበብ ካደረገው ዲስኩር መሃከል፣ ብዙ ትችትና ውግዘት ሊሰጡባቸው የሚችሉ በርካታ ጉዳዮች እንዳሉት ይታወቃል። በርካታ ሚድያዎች ብዙዎቹን ጉዳዮች እያነሱ እያፍተለተሏቸው ይገኛሉ። እዚህ ላይ እኔ ትኩረት ከማደርግባቸው ነጥቦች መሃል አንዱ አብይ አህመድ ስለባንዳነት ስለከሃዲነት ባደረገውና እጅግ ባስገረመኝ ዲስኩር ላይ። ይህ ብቻ አይደለም። የግል ጉዳይም አለኝ። ሌላው ደግሞ አብይ አህመድ በዚህ እለት ንግግሩ “ጉልበታቸው መዛሉን እድሜያቸው መግፋቱን ያልተገነዘቡ ካገር ወጥተው በለመዱት የመቃወምና የመላላክ መንገድ ቀጥለውበታል” ብሏል።፣ አብይ አህመድ ይህን ሲል ስሜን በቀጥታ አልጠቀሰም። ባይጠቅስም አብይ ግራዋ እንደጋቱት ሰው በዚህ መንገድ እየተንገፈገፈ ሊናገራቸው የሚችሉ በርካታ አዛውንቶች በውጭ እንደሌሉ አውቃለሁ። ይህ ብቻ ሳይሆን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር እንዳበቃ፣ ራሱ ያደራጀው የሚድያ ስራዊት፣ የአብይን ንግግር ሲያብራራ፣ በምሳሌነት እንዲያቀርብ የተነገረው እኔን መሆኑን ማወቅ ስለቻልኩ ንግግሩ እኔን የሚመለክት ለመሆኑ ጥርጣሬ እንዳይኖረኝ አድርጎታል። የዲጂታል ሚድያውም የተሰጠውን ተልእኮ ተቀብሎ የሚችለውን ሁሉ እየሰራ ነው። ለማንኛውም ይህ የአብይ እዲጂታል ሰራዊቱድርጊቶች ደህና አርፎ የነበረውን ብእሬን እንዳነሳ ያደረጉኝ ጉዳዮች እነዚህ ናቸው። አብይ አህመድ የሚባል አምባገነን፣ ለባንዳነትና ለክሀደት፣ የተመቻቸ የአእምሮ ውቅር፣ የማንነት ሃረግ፣ የታሪክ መስረት ያለው ሰው መሆኑ ይታወቃል። የእወቀትና የልምድ ውሱንነት ያለው መሆኑ ከራስ መተማመን ማነስ የሚመነጭ ለባንዳነትና ለተላላኪነት በቀላሉ የሚያጋልጠው ተፈጥሮ ያለው ሰው ያደርገዋል። በተግባርም፣ ደግሞ ዳጋግሞ ሃገርን፣ ህዝብን፣ ወዳጆቹን፣ ቅርቦቹን፣ እውቆችን የካደ ሰው ነው። ታዲያ እንዴት ሆኖ ነው እንደዚህ አይነት ፍጥረት በድፍረት ስለክህደት፣ ስለባንዳነትና ስለቃል ማጠፍ፤ የሞራልና የስብእና ልእልና ያለው ሰው ይመስል በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ዲስኩር ለመስጠት የደፈረው። የሚመልስልኝ የለም ብሎ? ነገሩ ሁሉ አንቺው ታመጭው ስልሆነ እስኪ አናሩጠው። አብይ አህመድ የኤመሬቱ ገዥ የመሃመድ ቢንዛይድ ጀለቢያ ውተፍ ነቃይና ተላላኪ መሆኑ ይታወቃል። አብይ ከመሃመድ ቢንዛይድ መመሪያ ይቀበላል፣ ቀጠናው በመሃመድ ቢንዛይድ ትእዛዝ ይበጠብጣል። ኢትዮጵያን የመሃመድ ቢንዛይድ የፖለቲካ ሺሻ ማጨሻ እቃ ካደረጋት ስንብቷል። ከእርግዝና መከላከያ ጋር የተያያዘውን ሌላ ቃል ያልተጠቀምኩት፣ የአንባቢን ስሜት ላለመንካት ነው። አብይ “ለአሜሪካ ስሰልል ነበር፣ ዛሬም ቢሆን ለአሜሪካ ራሴን እሰዋለሁ” ብሎ በአደባባይ ለጋዜጠኛ ለመናገር የደፈረ የመጀመሪያው የአንድ ልኡዋላዊ የሆነ ሃገር መሪ ነው። የመጨረሻውም ሳይሆን አይቀርም። በተላላኪነትና በባንዳነት መሰለፍን፣ መለመንን ለምኖ ምጽዋት ማግኘትን ልዩ ጸጋ እና ችሎታአድርጎ የሚመለከት ሰው ነው። ራሱን አዋርዶ ኢትዮጵያን የሚያክል ትልቅ ሃገር ያዋረደ ግለሰብ ነው። ይህ ግለሰብ ሌሎችን በባንዳነት ሲከስ፣ በተላላኪነት ሲወነጅል ትንሽ አፉን ያዝ አያደርገውም። የሃገሬ ሰው “ተናግሮ ከሚያናግር ይሰውርህ” ይላል። ይህ ምርቃት ስላልደረሰኝ ለእዚህ አብይ አህመድ ለሚባል ደፋር፣ "ቃል መጠበቅ ፣ አለመክዳት፣ ባንዳና ተላላኪ አለመሆን" ማለት በተግባር ሲገለጥ ምን እንደሚመስል እሱ ራሱ ከሚያውቃቸው ሃቆች በመነሳት ትምህርት መስጠት ተገቢ ሆኖ አግኝቸዋለሁ። ከታች የምታይዋቸው የቪዲዮ ክሊፖች አንዱ፤ የመጀመሪያው አብይ አህመድ “ አንተ ካልተፈታህ ስራዬን እለቃለሁ ብዬ አስፈታሁ” ብሎ ቢሮው ጠርቶ ባነገረኝ (በኋላ ውሸት መሆኑን አረጋጫለሁ) እለት፣ ከአራት አመት እስራት በኋላ ከእስር በተለቀቅኩ ማግስት፣ ግንቦት 22 2010 ቀን የተናገርኩት ነው። ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስና የቻይና ሚድያ (CGTN) በእንግሊዝኛ ቋንቋ የሰጠሁት ቃለ መጠይቅ ነው። ትርጉሙ፤ “የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር፣ ለመቀራረብና ለመደማመጥ የሚያበረታታ ነው። እውነተኛ ለሆነ የፖለቲካ መስተጋብር ግን በርካታ ነገሮች መስተካከል አለባቸው። ተጨባጭ የሆኑ ስራዎች መሬት ላይ መሰራት አለባቸው። የፖለቲካን እስረኞችን መፍታት ብቻ በቂ አይደለም። ጥሩ ንግግር ማድረግ ብቻ በቂ አይደለም። እዚህ ሃገር ውስጥ፣ በፖለቲካው፣ ተጨባጭ ከሆኑና መሰራት ካላባቸው ጉዳዮች ውስጥ የነጻና ገለልተኛ ተቋማት የመቆማቸው ጉዳይ ወሳኝ ነው። በሌሎች የማህበራዊና የኢኮኖሚ ዘርፎችም መቃለል የሚጠይቁ ችግሮች አሉ። እኛ የመቃወም ሱስ የለብንም። የምንቃወም ክሆነ፣ መቃወም የሚጠይቁ ጉዳዮች ስላሉ ብቻ ነው። ለመቃወም ብቻ ስንል አንቃወምም። አወንታዊ ጉዳዮች ካሉ የማናመሰግንበት/የማናደንቅበት ምክንያት የለም። በጎ ያልሆኑ ነገሮች ከተከሰቱ፣ አፋኝነት ከመጣ ከህዝብና ከሃገር ጥቅም ጋር የሚጻረሩ ስራዎች ከተሰሩ መቃወም ብቻ ሳይሆን አምረን የምንቃወም ይሆናል። ለሁሉም መልካም ጅማሮ ነው።” የሚል ነው። ከዛን እለት ጀመሮ በግሌ ለአብይ አህመድ በቀጥታ በዋትስአፕ ቻት፣ በሰነዶች፣ በአካል በተገናኘንባቸው በርካታ አጋጣሚዎች በጎና በጎ ያልሆኑ አመለካከቶቹን እና ድርጊቶቹን ያለምንም አድርባይነት ለመጠቆም ሞክሪያለሁ። ሁሌ አሉታዊ ትችቶችን ማቅረብ ብቻ አይደለም። በጎ ጅማሮች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማበራታት ሞክሬያለሁ። በድጋፍም ደረጃ ቢሆን አብይ አህመድ ቀጣፊ መሆኑን ሳልረዳ፣ እንደ ታዬ ደንዳ አይነቶቹ ስለስሜን እዝ መጠቃትና በጥቃቱ የአብይ ሴራ ምን እንደነበር ሳይነግሩን፣ ወያኔዎችን ሙሉ በሙሉ ወንጀለኛ አድርጌ በማየት፣ የአብይ መንግስት በወያኔ እንዳይሸነፍ ከጎኑ ቆሜ ድጋፍ ሰጥቸዋለሁ። በተኙበት ወያኔ ጨፈጨፋቸው ተብሎ ለተነገሩን የሰራዊቱ አባላት ቤተሰቦች መቋቋሚያ መጽሃፍ ሸጬ ካገኘሁት ገንዘብ ላይ 100 ሸህ ብር ለግሻለሁ። ይህ የአብይ አህመድ ሰራዊት ግን ዛሬ በአማራ ክልል የልጆቻችንን የእህቶቻችን ጡት ይቆርጣል። ይህ እንዳለ ሆኖም በበኩሌ በ2010 አ.ም “የመቃወም ሱስ የለብንም የሚለውን አባባሌን ከሚገባው በላይ በመለጠጥ ድጋፍ መስጠት ሊቋረጥ የሚገባበትን ወቅት ማየት እንዳልችል ባደረገ ሆደ ሰፊነት ለአብይ መንግስት ድጋፍ እንደሰጠሁ የሚያሳይ ነው። ቃል መጠበቅ ይህ ነው። በተለጠፈው ቪድዮ ላይ “መንግስት ማፈን ከጀመረ፣ የህዝብን እና የሃገርን ጥቅም ተጻሮ የሚቆም ከሆነ መቃወም ብቻ ሳይሆን አምረን እንቃወመዋለን” ብዬ ነበር። ነገሮች እየተበላሹ ሲመጡ፣ የደህነነት ቀውሱ እየጨመረ፣ አፈናው፣ እልቂቱ፣ መፈናቀሉ እየተበራከተ፤ ዘረፋው እየተስፋፋ፣ መንግስት ለማይፈጽማቸው ሃላፊነቶቹ የሚሰጣቸው ሰበቦችና ምክንያቶች አጠራጣሪ መሆን ሲጀመሩ፣ “ይህ መንግስት የከፋ አገዛዝ ወደመሆን እያኮበኮበ ነው” የሚል ስሜት ሲቀሰቅስብኝ፣ ምልከታዬን በውስጥ ማቅረብ ይሻላል” በሚል ብዙ ነገሮች እንዲታረሙ ተቃውሞዬን በቀጥታ ለአብይ አህመድ አቅርቤያለሁ። ሆኖም ግን ይህ በውስጥ የሚቀርብ ምልከታ ለአብይ አገዛዝ የተመቸው እንደሆነ፣ ሰውየው በአንድ ጆሮ ሰምቶ በሌላው የሚያፈሰው መሆንን መረዳት ስጀመር፣ በአደባባይ በበርካታ መድረኮች፣ የአገዛዙን አደገኛ አካሄድ በንግግር በጽሁፍ ተችቻያለሁ። ሁለተኛው ቪዲዮ 2013 አልቆ 2014ን ለመቀበል በተዘጋጀ በአል ላይ የተናገርኩትና በኢሳት ቴሌቪዥን ለህዝብ የተላለፈ ነው። ንግግሩ በቀጥታ የሚመለከተው፣ በኦሮሞ ብልጽግና ባለስልጣናትና የቅርብ ደጋፊዎቻቸው ዘንድ እየተስፋፋ የመጣውን የተረኛነት ስሜትና፣ የዘር የስልጣን እና የጥቅም ትስስር፣ በከተማው ውስጥ እየታየ ከመጣው አይን ያወጣ ዘረኛነት ጋር ተያይዞ ያደረግሁት ነው። የሙስናው ጉዳይም ከመቼው ዘመን በከፋ መልኩ ስር እየሰደደ እንደሆነ መረጃ በማሰባሰብ ላይ ተመስርቼ የተናገርኩት ነው። ሁሉንም ጽሁፌን ንግግሬን ከማንም አስቀድሜ ለአብይ አህመድ እንዲደርሰው ሳደርግ ነው የኖርኩት፤ አላየሁትም እንዳይል። አሁንም ይህ በሁለተኛው በቪዲዮ ያቀረብኩት ንግግር በ2010 ከእስር በተፈታሁበት ቀን ካቀረብኩት ንግግር ጋር ማነጻጸር ይቻላል። “የምንቃወመው ዝም ብለን ለመቃወም አይደለም፣ መቃወም የሚያስፈልጉ ጉዳዩች ሲኖሩ ነው” ላልኩት ማረጋገጫ ነው። ይህ ንግግር ትልቅ የተቃውሞ ንግግር አልነበረም። በወቅቱ ማንንም ሰው ይህን ንግግር፣ ዝቅተኛው በመንግስት ላይ ሊቀረበ የሚችለው ትችት እንደሆነ የሚገንዘብ ይመስለኛል። ከዚህ ንግግር ውጭ በርካታ በሚገባ የተጻፉ ትችቶቼን በፌስ ቡክ ገጾች በየጊዜው አደባባይ አውጥቻለሁ። የመጨረሻውና በተፈታሁ እለት የተናገርኩትን “አፋኝ እና ጸረ ህዝብና ጸረ ሃገር ተግባራት መንግስት ከፈጸመ አምረን እንታገለዋለን” ያልኩት ደረጃ የደረሰ ጉዳይ መምጣቱን የሚያሳየው ነጥብ ነሃሴ 17 2015 አ.ም. የአብይ አህመድ አገዛዝ የአማራን ክልል በወታደራዊ እዝ አገዛዝ ስር ያስገባበትን አዋጅ ተከትሎ የጻፍኩት ነው። በፌስ ቡክ “ መሆን የነበረበት ወያኔን ጠበቅ አማራን ለቀቅ ማድረግ ነበር” በሚል ርእስ ከጻፍኩት የተወሰደ ነው። “በአማራ ክልል እየሆነ ባለው እጅግ አሳዛኝ ሁኔታ ላይ የዛሬውን የግል ምልከታዬን ሳቀርብ ከላይ በአንቀጽ 5 እና 6 ገደብ የሌለው (በእለቱ የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እያጣቀስኩ ነው) ስልጣን የተሰጣቸው አካላት በእኔም ይሁን ከእኔ ጋር ቅርበት ባላቸው አካላት ላይ ማንኛውንም እርምጃ ሊወስዱ እንደሚችሉ እያወቅሁ ነው። በሌሎች ግለሰቦች ላይ እንዲህ አይነቱ እርምጃ እየተወሰደ እንደሆነ መረጃው እየደረሰኝም ነው (እስራት፣ አፈና ድብደባ ማለቴ ነበር)። በእንዲህ አይነቱ ወቅት ዝምታን ያልመረጥኩት፣ በመንግስት ወንጀለኛ ሆኖ ከመታየት ይልቅ በራሴ ህሊና ወንጀለኛ ሆኖ መታየት የበለጠ የሚያስጨንቀኝ ሰው በመሆኔ ብቻ ነው። ከጥቂት ቀናት በፊት ጌታቸው ረዳ፣ ዴንቨር ኮለራዶ ላይ ከ200 ሽህ በላይ ለውጊያ የተዘጋጀ ሰራዊት እንዳለው ተናግሯል። በዚህ ሰራዊት የተማመነው ጄነራል ጻድቃን "የማእከላዊ መንግስቱ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ቃል በገባልን መሰረት የትግራይን ግዛቶች ማለትም ወልቃይትን እና ራያን የማይመልስን ከሆነ በጉልበት እናስመልሳለን" ብሎ እዛው አሜሪካን ውስጥ በተዘጋጀ ስብሰባ ላይ ተናግሯል። ጻድቃን “ቃል ተገብቶልናል” ስለሚለው ጉዳይም ይሁን ስለጉልበት መጠቀሙ የሚናገራቸው ነገሮች ዝም ብሎ እንዳልሆነ ከህወሃት ከራሱ ስናገኛቸው የነበሩ በቂ መረጃዎች እንዳሉ የመንግስት ባለስልጣናት ያውቁታል። እነዚህ ሁለት ግለሰቦች ከየትኛውም የወያኔ አመራር በተለየ በጦርነቱ ወቅት “ከአማራ ህዝብ ጋር ሂሳብ እናወራርዳለን” በማለት በአደባባይ የተናገሩ ፣ የአማራ ህዝብ የተጨፈጨፈበትን፣ ሰው ብቻ ሳይሆን እንስሳቱ በጥይት የተቆሉበትን፣ ክልሉ ከስልጣኔ ርቆ ወደ ድንጋይ ዘመን እንዲመለስ ተደርጎ የመሰረተ ልማት ግንባታዎቹ፣ የህዝብ የአገልግሎት ተቋማቱ እንዲወድሙ የተደረገበትን፣ የፕሮፓጋንዳና የጦር እስትራተጂ የነደፉና ያስፈጸሙ ናቸው። (አንባቢ ይህን ሃቅ ዛሬ ጌታቸውና ጻድቃን የት እንዳሉ ራሱን እየጠየቀ እንዲያየው ያስፈልጋል) የሚገርመው ግን የታሪክ ቧልት የሚል ትርጓሜ ሊያሰጠው በሚችል ደረጃ፣ ጌታቸውና ጻድቃን፣ የአንደኛ ደረጃ የአውሮፕላን ቲኬት ተቆርጦላቸው፣ ሲኦል ድረስ ወርደንም ቢሆን እናወድመዋለን ባሉት የኢትዮጵያ መንግስት፣ የቪአይፒ እንክብካቤ ተደርጎላቸው ወደ አሜሪካ ተጉዘው፣ በከፍተኛ እብሪትና መንደላቀቅ ስለሰራዊታቸው አቅምና ስለቀጣይ ጦርነት፣ ስለትግራይ አሸናፊነት በአሜሪካን ከተሞች ሲደሰኩሩ፣ ሲዘፍኑ፣ እስክስታ ሲወርዱ፣ ከሀገር ያሸሹትን ሃብት (ይህ ጻድቃንን እንጂ ምሽኪኔታን ጌታቸውን አይመለከትም) ቦታ ቦታ ሲያስይዙ፣ ከአሜሪካን መንግስት ጌቶቻቸውና እመቤቶቻቸው (ከነሱዛን ራይስ ) ጋር ሴራ ሲሸርቡ ከርመው በክብር ወደ መቀሌ ተመልሰዋል። በሌላ በኩል እነዚህ ግለሰቦች በአሸናፊነት ስሜት መናገሻ ከተማቸው በገቡ በቀናት ልዩነት፣ የእነዚህን እብሪተኞች ሃገር የማፍረስ ተልእኮ በመመከት፣ በስልጣን ላይ ያለውን መንግስት መንበር በማጽናት፣ በተኛበት ለተጨፈጨፈው የሃገር መከላከያ ሰራዊት አለኝታ በመሆን፣ በንብረቱ፣ በደሙና በአጥንቱ በህይወቱ መስዋእትነት የከፈለው የአማራ ህዝብ በወታደራዊ አገዛዝ ስር እንዲወድቅ ተፈርዶበታል። ይህን ካልኩም በኋላ ጽሁፌን የደመደምኩት እንዲህ ብዬ ነበር። “አሁን በአማራ ክልል ከልዩ ሃይሉ መፍረሰ ጋር ተያይዞ የተፈጠረውን ችግር ፣ ወያኔዎች ሲያደርጉ እንደኖሩት፣ የክልሉን መሪዎች በስልጣን እና በጥቅም በመደለል፣ ህዝቡንም ሆነ አንዳንዶቹን ከህዝቡ ጎን ለመቆም የወሰኑትን የአስተዳደርና የጸጥታ አካላት በማስፈራራት፣ ወይም ከእውነታው ጋር በተጣላ የፕሮፓጋንዳ ውርጅብኝና (በወረዳ ሶስት ሽፍቶች የሚለውን የሰሞኑን የአብይ አባባል ልብ ይሏል) በሌሎችም ዘለቄታዊ መፍትሄ ማምጣት በማይችሉ መንገዶች ሄዶ ለማቃለል የሚደረግ ሙከራ የትም እንደማያደርስ መታወቅ ይኖርበታል።” በመጨረሻም የሚያዳምጥ ካለ፣ “እንዲህ አይነት ችግር በኢትዮጵያ ውስጥ ሲከሰት የመጀመሪያው አይደለም። የመጨረሻውም ላይሆን ይችላል። እንዲህ አይነት፣ በተለይ ከእውነተኛ የህዝብ ብሶት ጋር የተያያዙ ችግሮች ሲፈጠሩ፣ ችግሮቹን ለመፍታት በተለያዩ ዘመናት ያለፉ መንግስታት ከሄዱበትና ውጤት ካላመጡ አደገኛ አካሄዶች መማር ተሸናፊነትን ሳይሆን ብልህነትን የሚያሳይ ይሆናል።” እላለሁ። ይህ ጽሁፍ በተጻፈ በ15ኛው ቀን፣ ኢትዮጵያን ለቅቄ፣ ንብረትም መኖሪያ ቤትም ወደ አልነበረኝ እንግሊዝ ሃገር ጉዞየን ጀመርኩ። ለማጠቃለል አብይ እንደሚለው ሳይሆን፣ እኔ አቅሜ መዛሉንም፣ እድሜየ መግፋቱን የጠፋኝ ሰው አይደለሁም። ችግሩ እኔ አቅሜን ካላማወቄ ጋር የተሳሰረ ሳይሆን ከራሱ ከአብይ የአመለካከት ችግር ጋር የተይያዝ መሆኑን መረዳት አልቻለም። ማንም ሰው ሺ ጊዜ ጉልበቱ ቢዝል፣ እድሜው ቢገፋ በምርጫው ካልሆነ በቀር፣ ለአብይ ባሪያ ወይም ገረድ ሆኘ ከመቅረት የሚያድነው አቅም ሁሌም እንደሚኖረው አብይ ማየት አልቻለም። አብይ አህመድ፣ ሁሉም ሰው በየጊዜው ሰበብ እየፈጠረላቸው እንደሚስድባቸው እንደ ብርሃኑ ነጋ፣ እንደ አርጋዊ በርሄና እንደ ቀጀላ መርዳሳ ይመስለዋል። እብይ ነው በምሳሌነት የሚያነሳቸው እኔ አይደለሁም። “ጉልበቴ ዝሏል። እድሜ እየገፋ ነው። አብይ ለምን ሚሊዮኖችን አይገድልም፣ አያፈናቅልም፣ አያሳድድም፣ ለምን እስር ቤቶች በንጹሃን እስረኞች ሞልተው አይተርፉም። ለምን ሃገር እስከ አጥንቷ በዘራፊዎች አትጋጥም። ለምን መቶ ሺ እናትችና እህቶች አይደፈሩም። ለምን የሴቶች ጡት አይቆረጥም፣ ህጻናትና አረጋዋያን አይጨፈጭፍም። ምን አገባኝ።” ብለው የተስጣቸውን የስልጣን እና የጥቅም ፍርፋሪ እየለቀሙ መኖር የማይችሉ አዛውንቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ አብይ ለመረዳት ስሪቱ ሊፈቅድለት አልቻለም። የአብይ አህመድ መሰረታዊ የፖለቲካ ፍልስፍና በጥቅምና በስልጣን የማይደለል ሰው አይኖርም ነው። “እርካብና መንበር” የሚል ርእስ የሰጠው መጽሃፉ፣ አብይ ዛሬ የሚያደርጋቸውን ድርጊቶቹን የቀረጹትን አስተሳሰቦቹን በሚገባ ዘርዝሮ ያስቀመጠበት ዋናው መጽሃፍ ነው። "መደመር" አይናችሁን ጨፍኑና ላሞኛችሁ በሚል ስሌት የተጻፈ ቅጥፈት ነው። "ስልጣን እና ጥቅም፣ የአንቱታ፣ የትልቅነትና የአዋቂ ነዎት ፉገራ የማያታልለው ሰው የለም" የሚል እምነቱን አብይ አህመድ በዚህ መጽሃፉ ውስጥ ደግሞ ደጋሞ ያቀረበው ጉዳይ ነው። አብይ ይህን እምነቱን አድማሳዊ እውነት አድረጎ የተቀበለ ሰው ነው። አብይ ይህን ሁሉንም ሰው “በሬ ሆይ እያልኩ ስልጣን እና ጥቅም እያሳየሁ ባሪያ አደርግሃለሁ” በሚል የያዘውን ጽኑ የፖለቲካ እምነት የሚጻረር የሰዎች አቋም ሲያጋጥመው እንደ ግራዋ ይመረዋል። “ማንጎ ነኝ ብለው የሚያስቡ ግን ግራዋ የሆኑ” በሚል ባላፈው እሮቡ በፓራማ ስብሰባው ወቅት ግራዋ እንደጋቱት ሰው ተንገፍግፎ የተናገረበት ምሬት ምንጩ ይህ ብቻ ነው። ይህን ስል እኔ ማንጎ ነኝ እያልኩ እንዳልሆነ ይታወቅልኝ። Abiy Ahmed Ali 🇪🇹 AA. PROSPERITY PARTY Neamin Zeleke Dawit እስከዳር እምሻው 🇪🇹አስካለ ማርያም Ephrem Madebo Elizabeth Altaye @yeabatuli

Andargachew Tsege

11,793 просмотров • 10 месяцев назад

የመሪ ስነ-ልቦነናና ዶክተር አብይ! Abiy Ahmed Ali 🇪🇹 ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በዚህ 8 አመት የተፈተኑትን ያህል ባለፉት መቶ አመታት የነበሩ የኢትዮጵያ መሪዎች እንዳልተፈተኑ እርግጠኛ ነኝ። ሶማሌ ክልል ከነበረው አመፅ ጀምሮ በየቦታው ሁን ተብልው የተለኮሱ የብሔር ግጭትና ጥቃቶች፣ በየቅያሱ የፈላው አማፂ ብዛት፣ ሰፋ ላለ ግዜ የተደረገው የትግራዩ ጦርነት፣ ጂኦፖለቲካው፣ የሶማሊያና የሱዳን አለመረጋጋት፣ የውጪ ሃይል ጣልቃ ገብነት፣ ወዘተ ተቆጥሮ አያልቅም። እውነተኛ መሪ የሚለካው በፈተናው ልክ ነው። ኖርዌይን የሚመራም ኢትዮጵያን የሚመራም በእኩል አይን መታየት የለበትም። ኢትዮጵያን መምራት አምስት የተረጋጉ ሐገራትን ከመመምራት ይበልጣል። አንድ መሪ በተቻለ መጠን ወታደራዊ ባክግራወንድ ቢኖረው ጥሩ ነው ይባላል። ሐገር በፈተና ስትናጥ ተረጋግቶ ውሳኔ መስጠት እንዲችል ወታደራዊ ስነልቦና የግድ ይላል። ኢትዮጵያን ከዩኒቨርስቲ እስክሪብቶ ብቻ ይዘህ ወጥተህ በቀላሉ የምትመራት ሐገር አይደለችም። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ባይሆኑ ኖሮ ሐገራችን አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በገባች ግዜ ተረጋግቶ ሐገርን ማስቀጠል ለብዙ ሰው የሚቻል ነገር አይመስለኝም። የማርቆሱ የአውሮፕላን ማረፊያ የሚነግረን ይሄንን ነው። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ባቡር አይቆምም። ጠላት እፏልልበታለሁ የሚልበት ምድር ሄደው ትልቅ ፕሮጀክት ተክለው መርቀው ይመለሳሉ። ሰላም በራቀበት ቦታ ሰላሙን ማስጠበቅ አንድ ነገር ሆኖ እዚያው ቦታ ላይ ፕሮጀክት ጨርሶ ሄዶ መመረቅ ሌላ አቅም ይጠይቃል። በሌሎች አካባቢዎችም፥ በተለይ የፀጥታ ችግር አለባቸው በሚባሉባቸው አካባቢዎች ልማቱ አልተቋረጠም፣ ፕሮጀክቶች ተቀርፀው መሬት ላይ ይወርዳሉ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽ ሚሰጡት በስራ ይመስላል። loud minority ዎች ድምፃቸው ጎልቶ ስለተሰማ በጫጫታ ሐገሩን የተቆጣጠሩ ይመስላሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ መሃላቸው ሄደው አይናቸው እያየ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ፈፅመው በስራ ምላሽ ይሰጣሉ። ይሄን ለማድረግ “መሪ” መሆን ይጠይቃል። አሜሪካ በታሪኳ የከፋውና አገርን ለሁለት የከፈለ የእርስ በርስ ጦርነት (American Civil War) ውስጥ በነበረችበት፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በሚያልቁበት አስቸጋሪ ወቅት። በግዜው መሪ የነበረው አብርሃም ሊንከን ጦሩን እየመራ የአሜሪካን ምሥራቅና ምዕራብ ጫፎችን የሚያገናኝ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ማይሎችንና አስቸጋሪ ተራሮችን የሚያቋርጥ ግዙፍ አህጉር አቋራጭ የባቡር መስመር (Transcontinental Railroad) እንዲጀመር አዘዘ። በግዜው ብዙዎች “አበደ” ብለውት ነበር። ሰላሙ ይቅደም ያሉም ነበሩ። እንዴት አሜሪካ ትሰንብት አትሰንብት ሳያውቅ እንዲህ አይነት እቅድ ያወጣል ያሉትም እልፍ ናቸው። ሊንከን ግን ጦርነቱን እየመራ በነበረበት በዚያ አስጨናቂ ወቅት፣ የባቡር መስመሩ የወደፊትዋን የተባበረች አሜሪካ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን ተገንዝቦ ነበርና ከአቋሙ ዝንፍ አላለም። በ1862 (ጦርነቱ በሃይል በተፋፋመበት ወቅት) ህጉን አጽድቆ፣ በገንዘብ እጥረትና በጦርነት ግርግር ሳይበገር ፕሮጀክቱ እንዲቀጥል ማድረግና አሜሪካን ማስተሳሰር ችሏል። ትክክለኛ መሪ በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ሁሉ ነገውን ይሰራል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድም እንዲሁ ዛሬን ሳይሆን ነገን ማየት የሚችሉ መሪ ናቸው። እንደውም አንድ ግዜ ውሃዋን በብርጭቆ ይዞ አካባቢው ባለው ነገር Diatracted ሳይሆንና ውሃዋን ሳያጎድል ከግቡ ያደረሰውን ሰው ታሪክ ተናግረው ነበር። ያ ሰው እራሳቸው ዶክተር አብይ ይመስሉኛል። ለማንኛውም እኔና ቤቴ ነውጥ በሚመስል ግርግር ውስጥ ለማይናወጡት መሪ እጅ እንነሳለን!

Natnael Mekonnen

12,421 просмотров • 1 месяц назад