Loading video...

Video Failed to Load

Go Home

ኢትዮጵያና ወደብ፣

38,617 views • 1 year ago •via X (Twitter)

11 Comments

samrawit 1215's profile picture
samrawit 12151 year ago

እኔም እንዳንተው ይቆጨኝ ነበረ 😭😭ይሄ ኢትዮጵያ ሀገራቺን በጠላቶችዋ ትመራእንደነበር ትልቁ ምልክት ነው መቼም ሃገሩን የሚወድ ለሕዝብ ወድፊት ዕጣ ፋንታ የሚጨነቅ አንድን ትልቅ ሀገር ባህርበር አልባ አያደርጋትም ያውም ለምኖ!!

Pan african Eritrean's profile picture
Pan african Eritrean1 year ago

Ethiopia was landlocked for centuries and there is no right you can claim for sea access for which you had not. International community has took note of your will irredentvism adventures already since in english you preach prace in local language you threaten and pose forconflict

heni berhane's profile picture
heni berhane1 year ago

የኦሮሙማው ኢሬቻን ቀይ ባህር ላይ አከብራለው ጥማት😂😂😂

Pan african Eritrean's profile picture
Pan african Eritrean1 year ago

International community must translate the amharic statements of Abiy Ahmed and should know that he brainwashes and pushes the Ethiopians for resentment and support for sea access by conflict against he says in english about peaceful and diplomatic sea access resolves.

Hassan Hassan's profile picture
Hassan Hassan1 year ago

You remind me what Meles said, " የ አክሱም ሀወልት ምኑ ነው ለ ደቡብ ህዝብ " Abiy's ambitious isn't for Ethiopia, but just to please his masters uae,

Pan african Eritrean's profile picture
Pan african Eritrean1 year ago

Posting such videos that posture irredentvisim and grabbing intention of others territory is against international laws. So if you mean it why do you come and boast as if you are something. You are nothing and like it or not will abide by international ruling.

Maximotopia's profile picture
Maximotopia1 year ago

የኢትዮጵያን ህዝብ ከአንድ ጦርነት ወደ ሌላ እያስገባህ የህዝብ ደሞ ትጠጣለህ በህዝብ ገንዘብ ትዘርፋለህ ደም መጣጭ አረመኔ! ከፍርድ አታመልጡም እየቀረበ ነው የፍርድ ቀን!

Yonas Ghebreab 's profile picture
Yonas Ghebreab 1 year ago

Dilution wake-up from dream Eritrea has never been part of Ethiopia at any point in history it was forcefully occupied by Ethiopia under the name of federalism by super powers and violating the federation to full annexation but the people of Eritrea regained its sovereignty

Alatash - አላታሽ 📌's profile picture
Alatash - አላታሽ 📌1 year ago

I don’t care if you gain port ownership through force but Tigray will not be a battleground for your ambition. You can fight them through Afar. Tigray will not support nor interfere your fight with Eri for Assab.

ሙኛኞ 🇪🇹's profile picture
ሙኛኞ 🇪🇹1 year ago

Ngl abiy is cooking here 😁

Solar Heavy's profile picture
Solar Heavy1 year ago

- All I Knew

Related Videos

ነሃሴ 2016 አብይ አህመድ በገዛ ወሬው የስከረ መሪ። የሚገርም ዘመን፣ ከዋናው የሃገር መሪ እስከ ተራው ካድሬ ምንም አይነት የሞራል ኮምፓስ የሌላቸው፤ የሞራል ልጓማቸው የተበጠሰባቸው ሆነዋል። የኢትዮጵያ ጉዶች ። እንዳንዴ ለእነዚህ ሰዎች አጓጉል ንግግር መልስ መስጠት እንደነሱ መሆን ነው በሚል ስጋት ዝምታ መምረጣችን የራሳቸውን ቅጥፈት እንደእውነት በመውሰድ በእብደት ህዲድ እንዲነጉዱ ከማድረጉ በላይ የእነሱን መበጥረቅ (ከኮሜዲያን እሸቱ መለስ የተማርኩት ዘመኑን የዋጀ ቃል) ጥቂቶችንም ቢሆን ማወናበዱ ስለማይቀር፣ ሁሌም ባይሆን አልፎ አልፎ የተመዘነና በቅጡ የታሰበበት ምላሽ መስጠት ተገቢ ሆኖ አግኝቸዋለሁ። ለዚህ ነው እየታከተኝም ቢሆን አልፎ አልፎ ብእሬን የማነሳው። 1. ሀተታ ላለማብዛት አጠቃላይ ከሆነው የሃገር ሁኔታ ልጀመር፤ “ኢትዮጵያ ብሄራዊ ደህንነቷን እና ጥቅሟን የሚያስጠብቅላት መንግስት የላትም። መንግስቷ በአንድ በራሱ ምስል በስከረና ባበደ አደገኛ ግለሰብ እጅ ወድቋል። ይህ በራስ ምስል አምልኮት የአእምሮ በሽታ የተጠቃ ግለሰብ ከኢትዮጵያ ጫንቃ ላይ ካልተነሳ ኢትዮጵያና ህዝቧ ብሄራዊ ደህንነታቸው፣ ጥቅማቸው፣ ሰላማቸው ብልጽግናቸው አይረጋገጥም ስንል ዝም ብለን እንደ አብይ አህመድ፣ እየተበጠረቅን አይደለም። ኢትዮጵያ መሬት ላይ ያለውን ሃቅ መሰረት አድርገን ነው። አብይ አህመድና ደንገጡሮቹ ግን ይህ ማየት ከማይችሉበት የተዘጋ የአእምሮ ውቅር ወይም ህሊና ገንብተው ተቀምጠዋል። መስማት ብቻ የሚፈልጉትን እየሰሙ፣ ማየት ብቻ የሚፈልጉትን እያዩ፣ ማመን ብቻ የሚፈልጉትን እያጠለሉ እያመኑ እንዲኖሩ ያደረገ፣ እውነታን በካደ የቅዥተ አዙሪት ውስጥ ወድቀዋል። እንደማይሰሙን ብናውቅም እስኪ ጥቂት እንበላቸው። ዝምታችን ለእብደታቸው የራሱን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ መፍቀዱ እኛንም ተባባሪ ያደርገናልና። የአንድ ሃገር ብሄራዊ ደህንነት ጥቅም የሚከበረው በመከላከያ ሰራዊቱ ነው። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ሰራው ዳር ድንበርና ሉአላዊነት ማስከበር መሆኑ ቀርቶ የአንድ ግለሰብ ስልጣን ለማስጠበቅ ሲል ከመላው የሃገሪቱ ህዝብ ጋር ተራ በተራ ወይም በአንድ ጊዜ ሲዋጋ መኖር፤ የገዛ የሃገሩን ልጆች መግደልና በነሱም መገደል እጣው ከሆነ ሰነበተ። ኢትዮጵያ በሁሉም አቅጣጫ ዳር ድንበሯ ተደፍሮ፣ መሬቷ በውጭ ሃሎች እጅ ተይዞ ይህን ማስቆም የሚገባው የመከላከያ ተቋም መሳሪያውን፣ የሰው ሃይሉንና መሉ ጉልበቱን በኢትዮጵያውያን ፍጅት የአንድን ግለሰብ የስልጣን ሱስ ለማርካት በስራ ላይ እንዲያውል ተደርጓል። የሰራዊቱ ጄነራሎች ለዚህ ታማኝነታቸው ቢሸጡት እስከ 500 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ መሬት ታደሏቸዋል፣ የሃገር ወርቅ ከየክልሉ መሪዎች ጋር በመሻረክ እያስቆፈሩ ከሃገር ውጭ ያወጣሉ፣ መሳሪያና መረጃ ለአልሸባብ ሳይቀር ይሸጣሉ፣ የግንባታ የንገድ ድርጅቶች፣ ከህንዶችና ከቻይኖች ጋር አቁመው ከሪል እስቴት አለፈው መለስተኛ ግድቦች ይገነባሉ። ለመከላከያ ከተመደበው ግዙፍ ባጀት የሚዘርፉትን እዚህ ላይ ማከል ነው። ሌላው የአንድ ሃገር የብሄራዊ ደህንነትና ጥቅም አስከባሪ ተቋም፣ የመረጃ የደህንነት ተቋሙ ነው። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ደህንነት ተቋም እንደተቋም መስራት ካቆመ ሰንብቷል። በሃሰት የትወልድ፣ የትምህርትና የማነንት መታወቂያ ማስረጃ፣ በዘመድ አዝማድ፣ በምልጃና በጉቦ የሚቀጥራቸውን ሰዎች እውነተኛ ማንነት መስሪያ ቤቱ ከማያውቅበት ደረጃ ላያ ደርሷል። ግለሰቦች በጠላት ሃገራት መንግስታትና ድርጅቶች ተመልምለው፣ በተቋሙ ውስጥ መተከላቸውን ወይም ከሰራተኞቹ መሃል ለጠላት ተመልምለው የሚሰሩ ከሃዲዎች እንዳይኖሩ የሚከታተል፣ በደህንነቱ መስሪያ ቤት ላይ የስለላ ስራ የሚሰራ ጸረ መረጃ የተባለው ክፍል ከደህነነት ተቋሙ ከጠፋ ስንብቷል። በዚህም የተነሳ አልሸባብ ወኪሎቹን በኢትዮጵያ የመረጃ መስሪያ ቤት አስቀጥሮ መረጃ መዝረፍ የቻለበት ሁኔታ ተከስቷል። ከመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች መሃል ምን ያህሉ አሁንም ለኢትዮጵያ ጠላቶችና መረጃ ለሚፈለጉ ሌሎች ተቋማት እንደሚሰሩ፣ መረጃ እንደሚሸጡ አይታወቅም። የመረጃ መስሪያ ቤቱ ከሱማሌው አልሸባብ እስከ ናይጀሪያው ቦኮ ሃራም አባላት የኢትዮጵያን ፓስፖርት በማደል በሃሰተኛ ስምና መረጃ በኢትዮጵያ ፓስፖርት በአለም ላይ መንቀሳሰ የሚችሉበትን ሁኔታ ፈጥሯል። ቀደም ብሎ ይደረግ የነበረው ሳምንታዊ፣ ወርሃዊ፣ የግማሽ መንፈቅ የመረጃ መስሪያ ቤቱ ግምገማዎች አይደረጉም። እቅዶችም የሉም። የሃገር አደጋ ትነተና አይቀርብም። የመረጃ ስራ የ24 ሰአታት ስራ መሆኑ ቀርቶ እንደማንኛውም መስሪያ ቤት ከሰአት በኋላ የስራ ሰአት 11 አንድና 12 ሰአት ላይ ሲያበቃ አብሮ ይቆማል። ከተማውና ሃገሪቱ በምሽት ያለደህንነት መስሪያ ቤቱ ክትትልና ቁጥጥር አድረው ይነጋላቸዋል። ሲመሸ የደህንነት መስሪያ ቤቱ የስራ ድርሻ በየጭፈራ ቤቱ እየዞሩ ባለቤቶቹን እያስፈራሩ መጠጣትና እንደማፍያ አለቆች የከለላ ክፍያ (protection fee) መሰብሰብ ሆኗል። የመስሪያ ቤቱ አለቆች በከፍተኛ ደረጃ የሚናናቁ፣ እርስ በርሳቸው የማይነጋገሩ፣ ሁሉም በግልና በቀጥታ ለእብዱ ጠቅላይ ሚኒስቴር ወሬ አቀባዮች ሆነዋል። የመስሪያ ቤቱ ሃላፊዎች ሙሉ ጊዚያቸውን እንደ መከላከያ ጀነራሎች በግል ሃብት ማካበቺያነት፣ የሃገርና የህዝብ ሃብት ዘረፋ ላይ የሚያወሉ ሆነዋል። ይህን የሚያደርጉት ደግሞ ልክ እንደ ወታደራዊ ጀኔራሎች በአለቃቸው በአብይ አህመድ እየታወቀ ነው። ታማኝ እስከሆኑ በየትኛውም የዘረፋ ስራ እንዲሰማሩ ፈቃድ ሰጥቷቸዋል። በርካታ ማስረጃዎች አሉን። ሌላው የሃገር ደህንነት ጠባቂ ተቋም የፌደራል ፖሊስ ተቋም ነው። ይህ የፌደራል ፖሊስ ተቋም እየከረረ በሄደ የዘር ክፍፍል የተወጠረ፣ ተቋማዊ አንድነቱ የተናጋ ነው። በዚህም የተነሳ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው በተለይ የአማራ ተወላጅ አባላቱ (የትግራይ ሰዎች ከመስሪያ ቤቱ ውስጥ ከጠፉ ቆይቷል) መሳሪያቸውን እንደያዙ የሚከዱበት ሁኔታ የተስፋፋበት ተቋም ነው። መሪዎቹ ከአደገኛ እጽ አንስቶ እስከ ከፍተኛ የኮንትሮባንድ ንግድ ውስጥ የተደፈቁ መሆናቸው ተደጋግሞ የተገለጸ ጉዳይ ነው። ባለፈው ሳምንት አብይ አህመድ ኮማንደር ፍቅሩ አለማየሁ ለሚባል የአዳነች አበቤ አጃቢ ለነበረ ግለሰብ በቀጥታ በምክትል ኮሚሽነርነት ማእረግ የአዲስ አበባ የወንጀል መከላከል ሃላፊ እንዲሆን የስጠው ሹመት “የዘር ኮታ ምደባውን የተጻረረ፣ የአማራን ቦታ ለኦሮሞ የሰጠ ነው” በሚል በተቀሰቀሰ ቁጣ 16 ዝቅተኛ መኮንኖችና ፖሊሶች እኛን አማሮችን በእዚህ ተቋም ውስጥ የሚወከለን የለም በሚል ምሬት መሳሪያቸውን ይዘው መሰወራቸው ታውቋል። የፌደራል ፖሊሲ ሃላፊዎች ዋናው ስራቸው በአብይ አገዛዝ ላይ ህዝብ እንዳያማጽ ከመጠበቅ ውጭ በሃገር ብሄራዊ ጥቅምና ደህነት ዙሪያ ከታዬ ዋናዎቹ የሃገር ጠንቆች ከሆኑ ሰነባብቷል። ሌላው የሃገር ጥቅምና ደህነነት ማስጠበቂያ ተቋም የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱና የዲፕሎማሲ ስራው ነው። ይህን መስሪያ ቤት በአብይ ተላላኪዎች ከመሞላት አልፎ የአብይ አህመድ የግል ፍላጎት ማስፈጸሚያ ከሆነ ቆይቷል። ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከታዬ አጽቀስላሴ በላይ ተሰሚነት ያላት ምክትሉ ብርቱካን አያና ናት። አምባሳደሮች የሚያደገድጉት፣ የተሻለ ምደባ እንዲያገኙ ጉቦና ስጦታ የሚሰጡት ለዚች የአብይ አህመድ የቅርብ ሴት ነው። የአብይ አህመድ እብደት በሚገባ የተገለጸበት፣ የሃገርና የህዝብ ደህንነትና ጥቅም ከፍተኛ አደጋ ላይ የወደቀበት የመንግስት እንቅስቃሴ ቢኖር የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ ነው። በተሳሳተ የአብይ አህመድ የውጭ ጉዳይ እንቅስቃሴዎች ኢትዮጵያ ከሁሉም ጎረቤቶቿ ጋር ተጣልታለች። ማንም በበጎ አይን የሚያያት የለም። ምንም ደሃ ብትሆን በቀጠናውና በአለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎምሲ መስኩ ትታይበት የነበረው የላቀ ስፍራዋ ላይ ዛሬ የለችም። ኢትዮጵያ ለደረሰባት ጉዳት ብዙ ምሳሌ ማቅረብ ቢቻልም ከሱማሌላንድ ጋር አብይ ገባሁ ያለው በቅጥፈት የተሞላ፣ ገና ከመጀመሪያ የትም እንደማይደርስ የተነበይነው የመግባቢያ ሰንድ ፊርማ ትልቁ ምሳሌ ነው። ሰነዱ በተፈረመበት ወቅት “ለሃገር ደህንነት አደገኛ ውሳኔ ነው” ብለን የተቃወምነው ግለሰቦች፣ አብይና አሽቃባጮቹ እንዳሉት ሃገር ሲያልፍላት አይናችን የሚቀላ ባናዳዎች ስለሆን አልነበረም። ይህን የሚሉት የባንዳነት ታሪክ በዘር ማንዘራችን እንደሌለ አጥተውት አይደለም። የሱማሌን ሉአዋላዊ ሃገርነት የሚጻረር ድርጊት በኢትዮጵያ ላይ ብዙ መዘዞች ያስከትላል ከሚል ተጨባጭ ስጋት በመነሳት ነበር ስምምነቱን ያወገዝነው። ለአንድ ሰሞን ህዝብን የማወናበድና የማፋዘዝ ፕሮጀክት ሲባል የተፈጸመ ድርጊት ኢትዮጵያ ሰራዊቷን ከሱማሌያ የምታስወጣበትን፣ አልሸባብ ኢትዮጵያ ድንበር ላይ ካምፕ የመሰረተበትን፣ ግብጽ በኢትዮጵያ ድንበር ሱማሌ ውስጥ ወታደሮቿን ማስፈር፣ የሱማሌን ሰራዊት ማሰልጠን የምትችልበትን፣ ቱርክ የሱማሌን የባህር ዳርቻዎች ደህንነት የምትጠብቅበትን ውሎች ከሶማሊያ ጋር መዋዋል የቻሉበትን ሁኔታ መፍጠር ችሏል። ህዝብ ለህዝብ መቀራረብ ጀመሮ በነበረው የኢትዮጵያና የሱማሌ ህዝብ ግንኙነት ላይ ያደረሰው ጉዳት ቀላል አይደለም። የመከላከያ የደህንነት ተቋማቷን አፍርሳ የተቀመጠችው ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲ መስኩ የሃገሪቱን ጥቅም ተጻረው ለሚቆሙ ሃገራትና መንግስታት፣ እድሜ ለአብይ አህመድ፣ የተመቻቸ ሁኔታ ፈጥራ አርፋዋለች። ሌላው የአንድ ሃገር ሉአላዊነት፣ደህነነትና ጥቅም ማስከበር የሚችለው ሃይል ከህዝብ አንድነትና በህዝብና በመንግስት መቀራረብ የሚገኘው ጉልበት ነው። የአብይ አህመድ አገዛዝ ሆን ብሎ የሃገሪቱ ህዝቦች እርስ በርስ በጎሪጥ እንዲተያዩ፣ ከዛም አልፈው እንዲጨፋጨፉ የሚሰራ መንግስት ሆኗል። በአብዛኛው የሃገሪቱ ህዝብ ላይ ጦርነት ከፍቶ ተጋጭቷል። አሁንም እየተጋጨ ነው። ከጦርነት በተረፈው ህዝብ ላይ የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሚል ስም የኢኮኖሚ ጦርነት ከፍቶ፣ ከጥቂት ባላሃብቶችና የመንግስት ባላስልጣናት በቀር የእያንዳንዱን ዜጋ ህይወት የምድር ሲኦል አድርጎት አርፏል። አብይ በፈጸማቸው ዘርፈ ብዙ ጸረ ህዝብ ድርጊቶቹ ከህዝብ ጋር ሆድና ጀርባ ሆኗል። ከሃገሪቱ የቆዳ ስፋት የሚቆጣጠረው እየጠበበ ሄዶ አገዛዙ እንደለቡ ያሻወን መፈጸም የሚችልበት ቦታ አዲስ አበባ ላይ ብቻ ሆኗል። አብይ አህመድ ህዝብንም ከሃገር ደህንነትና ጥቅም ማስጠበቅ ስራ አግሎታል። ኢትዮጵያ አደገኛ ሁኔታ ውስጥ ናት የምንለው ይህን ሁሉ ጉድ አይተን ነው። 2. ወደ ውቅታዊ ጉዳይ ስመለስ አብይ አህመድ የጫካ ቤተመንግስት፣ የኮሪደር ልማት፣ አዲስ ቱሞሮ (ጥራዝ ነጠቅ ስትሆን የሚመጣ የእንግሊዝኛ አጠቃቀም) እያለ የአልሞትኩም ብዬ አልዋሽም ፕሮፓጋንዳውን እራሱ እየሰራ፣ እራሱ እየተጋተ ሰከሮና ደንዝዞ መኖርን መርጧል። ይህን ድርጊቱን አያዋጣም የምንለውን በወሬ የምንኖር እራሱን በስራ የሚኖር አድርጎ መግለጽ ደግሞ የሰሞኑ የፐሮፕጋንዳ አቅጣጫው ሆኗል። ከዚህ ቀጥሎ የምላቸው ጥቂት ቃላቶች የአብይ አህመድ የሰሞኑ ጭኸቶች የቁራ ጭኸቶች እንደሆኑ የሚያሳዩ ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያልገባው እሱ የያዘው ስልጣን በአንዳንዶቻችን እጅ ቢገባ ለጫካ ቤተመንግስቱ አዲስ አበባ ላይ የሚያጠፋውን ከ10 እስከ 15 ቢሊዮን የሚደርስ ዶላር ከሱ በተሻለ ሃገርና ህዝብን ወደከፈተኛ ብልጽግና መውሰድ የሚያስችል ስራ ማዋል የሚችሉ ልጆች ኢትዮጵያ እንዳሏት ነው። አብይና አሽቃባጮቹን በምክን ያት ተከራክሮ ማሳመን እንደማይቻል በገባንም በህዝብ ፊት ማሳፈር ስለሚቻል 10 ቢሊዮን ዶላሩን እንዴት እንደምናጠፋው ቀጥሎ እናቀርባለን። 10 ቢልዮን ዶላሩን ምን እናደርገው እንደነበር ስንነግራችሁ የጫካው ቤተመንግስት፣ በግንባታ ወቅት የሚቀጥረውንና ከተገነባ በኋላ ስራ የሚፈጥርለትን የሰው ብዛት፣ ግንባታው ሲያልቅ የሚያስገኘውን የኢኮኖሚ ጥቅምና ሃገራዊ ፋይዳ በሚገባ ተመልክተን ነው።ዝርዝሩን ማቀረብ ያለበት አብይና ኩባንያው ነው። እኛ ማድረግ የምንችለው እንዲህ አይነቱ የጫካ ቤተመንግስት ኢንቨስትመንት ቱሩፋቶቹ ምን ይሆናሉ ብለን በመገመት ብቻ ነው። በተለይ ይህን ያህል ዶላር የፈሰሰበት ቤተመንግስት ሰላምና መረጋጋት በሌለበት ሃገር ቀርቶ ሰላም ቢኖርም ክወጭ የሚስበው ጎብኝ ይሁን በዚህ ቤተመንግስት ዙሪያ የሚገነቡ ህንጻዎች የሚስቡት የውጭ ኢንቨስትመንት እዚህ ግባ የሚባል የኢኮኖሚ ፋይዳ እንደማይኖር የታወቀ ነው። በግንባታ ስራውም ሆነ ካለቀ በኋላ የሚፈጥረው የስራ እድል ውሱን ነው። እንግዲህ ይህን አይነቱን በሃገራችን ከሚሰሩ ስራዎች ቅደም ተከተሉ እጅግ የተዛናፈን የዛሬ መቶ አመት እንኳን ሊሰራ የማይገባውን ስራውን እያመላከተ ነው አብይ አህመድ የስራ ሰው መሆኑን ሊነግረን የሚዳዳድው። እኛ ደግሞ ይህን በጫካ ቤተመንግስት ላይ አብይ አህመድ የሚያወጣውን ከ10 እስከ 15 ቢሊዮን ዶላር፣ በ10 ቢሊዮን ዶላር ገድበን ይህን ገንዘብ በሀሃገራችን ውስጥ ቅድሚያ ማግኘት አለባቸው ከምንላቸው ስራዎች አንዱ በሆነው የማዳበሪያ ኢንደስትሪ ምስረታ ላይ እንዴት እንደሚውልና ምን ሃገራዊ የኢኮኖሚ እርባና እንደሚኖረው በማሳየት አብይ የወሬ እንጂ የስራ ሰው አለመሆኑን ማሳየት እንችላለን። የማዳበሪያ ኢንደስትሪ ራሳችንን በምግብ ለመቻል፣ ከዛም አልፎ ግብርናውን መሰረት ያደረገ የኢንዱስትሪ አብዮት ለማስጀመር፣ በግብርና ምርታቸን ላይ የተመሰረተ የውጭ ምንዛሪ ችግራችንን መቅረፍ የምንችልበት እድል ለመፍጠር፣ በግንባታው ወቅትና ከተገነባ በኋላ የሚቀጥረውን የቋሚ ሰራተኛ ብዛት፣ ኢንዱስትሪው ራሱ የሚያመርተው ምርት ከሀገር ውስጥ ፍጆታ ተርፎ ወደ ውጭ ከሚላከው ምርት የሚገኘውን የውጪ ምንዛሪ ገቢ በአንድ ላይ ግምት ወስጥ አስገብተን የአብይን 10 ቢሊዮን ዶላር በማዳበሪያ እንዱስትሪ ምስረታ ላይ ብናውለው ምን ውጤት እናገኝ ነበር የሚለውን ጉዳይ ለአብይ አህመድና በዙሪያው ላሉ አሽቃባጮቹና በቅርቡ አዲስ አበባ ከተማን እናስውባለን በሚልፕሮፓጋንዳቸው ሊያደነዝዙት የፈለጉትን ህዝብ የሚከተሉትን ሃቆች እንንገራቸው። አብይ አህመድ ጫካ ቤተመንግስት የሚገነባባትን ገንዘብ ወደ ማዳበሪያ ኢንደስትሪ አዙሮት ቢሆን። 1. ለማዳበሪያ መስሪያ አስፈላጊ የሆነወን አሞኒያ የተባለ ኬሚካል በአመት በብዙ ሚሊዮኖች ሜትሪክ ቶን ማምረት ይቻል ነበር። 2. ለማዳበሪያ መስሪያ አስፈላጊ የሆኑትን ፎስፌትና ፖታሸ 1 እስከ 2 ሚሊየን ሚትሪክ ቶን በአመት ማምረት ይቻል ነበር። 3. ይህ የማዳብሪያ ኢንደስትሪ ኢትዮጵያ በአመት ለማዳበሪያ የምታወጣውን ከ800 ሚሊዮን እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ያሰቀር ነበር። 4. በውጭ የማዳበሪያ ኩባንያዎችና መጓጓዣዎች እንዲሁም በየጊዜው ከሚዋዥቅ የማዳባሪያ ዋጋ ራሷን ነጻ ማድረግ ትችል ነበር። 5. ዘመኑ የሚፈቅደውን የተራቀቀ ቴክኖሎጂ በማደበሪያ ማምርቻ ስራ ላይ ማዋል ትችል ነበር። 6. ይህ ዶላር በጥናትና ምርምር ላይ የተመስረተ ከማዳበሪያ ጋር የተያያዘ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የጥናትና የምርምር ተቋም እንዲኖረን ያስችል ነበር። 7. ለተፈጥሮ እና ለአካባቢ ጥበቃ እንብካቤ የሚያደርግ ኢንደስትሪ መገንባት የሚያስችል አቅም ይሰጠን ነበር። 8. በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞች፣ ኤንጂኔሮች፣ ኬሚስቶችም የፋብሪካ ማሽነሪ አንቀሳቃሾች፣ የማእድን ሰራተኞች፣ የድጋፍ ስራ የሚሰሩ ሌሎችንም በመቶ ሸዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች ስራ ያስገኝ ነበር። 9. የማዳበሪያው ኢንደስትሪ ትልቅነት የአለምን የማዳበሪያ ገበያ ከ5 እስከ 15 በመቶ የመቆጣጠር ትልቅ አቅም ሰለሚኖረው ኢንቨስትመንቱ ከኢትዮጵያ ውጭ በሌሎች ሃገሮች ሳይቀር መስሪያ ቤቶች የሚኖሩትና ሰራተኞችም የሚቀጥር ይሆን ነበር። 10. ኢትዮጵያ ለማደባሪያ መስሪያ የሚሆን ትልቅ የፖታሽ ክምችት ቢኖራትም፣ ለፖታሽና ለሌሎችም ለማዳበሪያ መስሪያ የሚሆኑ ወሳኝ ግብአቶችን ሩቅ ሳትሄድ ከጎረቤቶቿ ማግኘት የምትችልበትን የኢኮኖሚ ትብብር እድል የሚከፈት ይሆን ነበር። ከኤርትራና ከጅቡቲ ጋር ፎስፌትና ፖታሽ በማውጣት፣ ከደቡብ ሱዳን እና ከሱዳን ናይትሮጂን ለሚያስፈለገው የአሞኒያ ማዳበሪያ ለመስሪያ የሚሆነው የተፈጠሮ ጋዝ በመግዛት የሚፈጠረው የኢኮኖሚ መደጋገፍ ለቀጠናው ትልቅ ትርጉም ይኖረው ነበር። 11. ጥናቶች የሚያሳዩት በ10 ቢሊዮን ብር ኢንቨስትመንት የሚጀመር የማዳበሪያ ኢንደስትሪ ስራው ተጠናቆ በሙሉ አቅሙ ማምርት ሲጀመር ከ 5 ቢሊዮን እስከ 15 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ አመታዊ ገቢ ሊኖረው የሚችል ይሆናል፣ ከዚህ ውስጥ ትርፉ በየትኛውም ኢንደስትሪ ከሚገኝ ትርፍ የላቀ እንደሚሆን ይገመታል። 12. ይህ ስራ ለማስጀመር • የአሰሳና የአዋጭነት ጥናት ለማጥናት ከ50 እስከ 100 ሚሊዮን ዶላር፤ • የመስረተ ልማት ስራ ትልቁ ነው። የማእድን ማውጫ መሳሪያዎች፣ የማጓጓዣ ስራ፣ የኤነርጂ አቅርቦት፣ የውሃ አቅርቦት ስራ ከ500 ሚሊዮን እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ወጪ እንደሚኖረው ይገመታል። • ማእድን ማውጣትና ማጣራት ማምረት ፋብሪካዎችን ማቆም ከ 1 ቢሊዮን እስከ 2 ቢሊዮን ዶላር እንደሚፈጅ ይገመታል። • ለሎጂስትክ ለሃገር ውስጥና ወደ ውጭ ማጓጓዣ ከ300 ሚሊዮን እስከ 500 ሚሊዮን ዶላር፤ • አመታዊ የሰራተኛ ደሞዝ፣ የጥገና የመለዋወጫና ሌሎችም ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ መንቀስቃሰ እሰክሚችል ድረስ የሚያፈልገው ወጪ ከ 200 እስከ 500 ሚሊዮን ዶላር ይሆናል። አጠቃላይ የአንድ ትልቅ የማዳበሪያ ፋብሪካ የኢንቭስትመንት ወጪ ከ2 ቢሊዮን ዶላር እስከ 4 ቢሊዮን ዶላር እንደሚደርስ ይገመታል። ስራው አድካሚ ነው። በትንሹ አምስት አመታት ጊዜ ይወስዳል። እንደ ኮሪደር ልማት፣ እንደ ጫካ ፕሮጀክት በአዲስ አበባ ቤተመንግስቱ አካባቢ ለአብይ አይን ማረፊያነት የሚሰራ አይሆንም። አብይ ጠዋትና ማታ የሚጎበኘው፣ ውጤቱም በሚብለጨጩ ህንጻዎች በቀላሉ የማይታይ ስራ ነው። እንግዲህ ይህ ቁልፍና መሰረታዊ የሆነ የሃገርና የህዝብ ትልቅ ችግር ለመቅረፍ የሚያስፈለግ፣ ከዛም አልፎ በየአመቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ማስገኘትና ከፍተኛ ቁጠር ያለውን ቋሚ ሰራተኛ ለመቅጠር የሚያስችል አንድ የማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ከ 2 እስከ 4 ቢሊዮን ዶላር የሚጠይቅ ከሆነ፣ የጫካው ቤተመንግስት በሚሰራበት በ 10 ቢሊዮን ዶላር በአማካይ 3 ትልልቅ የማዳበሪያ ኢንዱስትሪዎች መገንባት ይቻል ነበር ማለት ነው። ይህን ኢንደስትሪ ለጫካው ከሚወጣው ወጪና የጫካው ፕሮጀክት ለሃገርና ለህዝብ ከሚሰጠው ፋይዳ ጋር ማነጻጸሩና የፋይዳወን ልዩነት የመገመቱ ስራ ለብልሁ የኢትዮጵያ ህዝብ እንተወዋለን። የአብይ አህመድ አገዛዝ የሀገር ጠንቅ ነው። ብልጭልጭ ፕሮጀክቶቹም የግለሰቡን ብኩን ስብእና የሚያሳዩ ናቸው የምንለው፣ በበልጽግና ዙሪያ አብይ እንደሰበሰባቸው የፓርቲው ደናቁርትና እነሱን እንዲያጅቡ አብይ ስልጣን ያጋራቸው እንደብርሃኑ ነጋ እንደ ግርማ ሰይፉ እንደነ በለጠ ሞላ ከአብይ እግር ስር እየወደቀን ጭራችንን የማንቆላው፣ በዘራችሁ አይድረስ ከሚል የመዋረድ እርግማንም ራሳችንን የምናድነው ጌታቸውና ፈጣሪያቸው አብይ እንደሚለው በወሬ ስለምኖር ሳይሆን፣ ለግል ስማችን፣ ክብራችንና ሆዳችን ሳይሆን ሃገርን የሚጠቅምና የሚጎዳ ተግባር ምን እንደሆነ ስለምናውቅ ነው። ይች በድህነት የተጨማደደች ሃገራችን እና በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠረው ደሃ ህዝባችን ወደ ብልጽግና የሚያመራው ጥቂት ከተሜዎችና ዳያስፖራዎች፣ አብይ እንዳለው ፎቶ መነሳት የሚችሉባቸውን ቦታዎች አዲስ አበባ ላይ ለመፍጠር ሲባል ብዙ ቢሊዮን ዶላሮችን በከንቱ በማባከን እንዳልሆነ ስለምናውቅ ነው። የከተማወን ህዝብ ረሃብ ለማስታገስ ማዳበሪያ ያለውን ትርጉም ስለምናውቅ ነው። ልኡላዊነትን አሳልፎ የሸጠ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ስራ ላይ እንዳናውል የሚያደርገንን፣ ከፍተኛ የሆነ የወጭ ምንዛሪ ፍላጎታችንን የሚቀንስ፣ ኢንደስትሪው ተጨማሪ የውጭ ምንዛሪ የሚያስገኝልን እንደሆነ ስለምናውቅ ነው። ግብርናን መሰረት ያደረገ የኢንደስትሪ አብዮት በማካሄድ አስተማማኝ ልማት ለህዝባችን ማጎናጸፍ እንደሚችል ስለሚገባን ነው። የአብይ አገዛዝ ያለበት ችግር በእውነት፣ በሃቅ፣ በእውቀት ላይ ተመስርተው ስካርና እብደቱን ከሚያመላክቱት ሰዎች ይልቅ እሱ የሚለውን እንደገደል ማሚቱ የሚያስተጋቡ፣ ወይም ለመጀመሪያ ጊዜ ከወንድ ጓደኛዋ ጋር እንደተዋወቀች አይና አፋር ለጃገረድ የሚሽኮረሞሙ ወራዶችን ማቅረቡ ነው። ከእነዚህ ሰዎች መሃል እኔ በግሌ የማውቃቸው በአንድ ወቅት ትልቅ ክብርና ግምት የሰጠኋቸው ሰዎች መገኘታቸው ነው፤ “እንዲህ አይነት ውርደት በዘራችሁ አይድረስ” እንድል ያሰኘኝ። አንዳርጋቸው ጽጌ Abiy Ahmed Ali 🇪🇹 FDRE Government Communication Service Mustafe M. Omer Al Ain Amharic አል ዐይን አማርኛ Ethiopian Reporter Sahle-Work Zewde Reuters Ethiopian Citizens for Social Justice #Ezema FDRE Ministry of Justice ኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር Al Jazeera English Billene ቢልለኔ Aster Seyoum Neamin Zeleke Office of the Prime Minister - Ethiopia BBC News (UK) DW Amharic Redwan Hussien Daniel Kibret Taye Atske Selassie Ethiopian National Dialogue Commission VOA Amharic Fana Media Corporation S.C. (FMC) @walta_info EBC WORLD እስከዳር እምሻው 🇪🇹አስካለ ማርያም Dawit

Andargachew Tsege

61,317 views • 1 year ago