Загрузка видео...

Не удалось загрузить видео

На главную

ጅግጅጋ ዳቦ ፋብሪካ ምርቃት

66,139 просмотров • 2 лет назад •via X (Twitter)

Комментарии: 7

Фото профиля Kelem.B
Kelem.B2 лет назад

በዘመኔ እንደ እናንተ አይነት ሰው በምድር ላይ መኖሩን በማየት እግዚአብሔርን እጅግ አመስግኜዋለሁ🙏🙏🙏

Фото профиля Dr. Ambachew Assefa
Dr. Ambachew Assefa2 лет назад

ጀግናው መሪያችን ዶ/ር አብያችን የጀግናው የጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ፣የአንጓዴ አሻራ የስንዴ ልማት በገበታ ለሀገርና ለትውልድ፣በታላቁ ህዳሴና ኮይሻ ግድብ በባህር በር ዘመቻ መሪ ሆነው ደሃን የሚያጎርሱ መሆንዎ ስናይ ጀግናና ደግ መሪ ነዎት አልን

Фото профиля Saba Shiferaw 🇪🇹(Abiy Ahmed Ali will lead )
Saba Shiferaw 🇪🇹(Abiy Ahmed Ali will lead )2 лет назад

ድንቅ ስራ በርቱልን

Фото профиля Abdallah A.
Abdallah A.2 лет назад

Jigjiga is Somalia.

Фото профиля ግ Z A ው
ግ Z A ው2 лет назад

Slowly but surly our future will be bright!! Thank you Prime Minister Dr. Abiy!

Фото профиля kie ቄ 🇪🇹
kie ቄ 🇪🇹2 лет назад

Inauguration of Jigjiga Bread Factory #Ethiopia

Фото профиля ላለይበላ
ላለይበላ2 лет назад

የአለማችን ብቸኛው ዳቦ ቤት የሚመርቅ ጠቅላይ ሚንስቲር 🤣🤣🤣🤣

Похожие видео

ቀናነት እና ምርቃት ========= ጉጠቶች ስለ አብቹ የሚያወሩትና የሚያስቡት እሱ በእውን ከሆነውና ከሚሰራው ጋር ፍፁም የማይገናኝ መሆኑን ለመረዳት ይሄ ቪዲዮ ሁነኛ ማስረጃ ነው። ዶ/ር አብይ ሀገሩን ይወድዳል! ይህን ደግሞ ከማንም በላይ የሚያውቁት እናቶች ናቸው። የኢትዮጵያ እናቶች የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሥራና ተግባር የሚለኩት ከስልጣንና ጥቅም አንፃር አይደለም። ከዚያ ይልቅ በልጆቻቸው የወደፊት ተስፋና ዕድል ነው። ሀገሩን የሚወድድ መሪ የእናቶችን ተስፋና ስጋት ይረዳል። ለልጆቻቸው የተሻለች ሀገር ለመገንባት ይጥራል። የኢትዮጵያ እናቶች ደግሞ የመሪያቸዉን ልብና ቀልብ ከባሎቻቸው እና ልጆቻቸው በተሻለ ይረዳሉ። በመሆኑም መሪያቸውን በአካል ሲያገኙት እንደ ልጃቸው ያዩታል፣ ከልባቸው ይሳሱለታል። ዘወትር ስለ እሱ ደህንነትና ጤንነት እንደሚጨነቁ የሚገልፁበት ቃል ሲያጥራቸው እምባ ይጨምሩበታል። እነዚህ እናቶች የኢትዮጵያ እናቶች ናቸው። የአማራ ህዝብ ማለት እነዚህ ናቸው። ይሄ የአማራ እናት እሳቤና አመለካከት ነው። በእርግጥ እነዚህ የወሎ እናቶች ናቸው። የሁሉንም እናቶች ቀናነትና ፍቅር ባውቅም የእነዚህ ደግሞ ትንሽ ለየት ያለ መሆኑን አልክድም። ዶ/ር አብይም "የእናንተ ደግሞ የተለየ ነው" ያለው ለዚህ ነው። አብችዬ ቀናነት ለራስ ነው። ለኢትዮጵያውያን ይበጃል ያልከውን ሁሉ በቀናነት ስትሰራ የእናቶች ፍቅርና ምርቃት ደግሞ እንዲህ በሄድክበት ሁሉ ይከተልሃል። Abiy Ahmed Ali 🇪🇹

Seyoum Teshome

33,020 просмотров • 2 лет назад

ጅግጅጋን እንደ ኃምሌ 28! ካለፈው ያልተማረው አብዲ ኢሌ ዛሬም ጅግጅጋንና መላ የሶማሌ ክልልን በደም ለማጠብ በህዝብ ህይወት ላይ ቁማሩን ቀጥሏል፡፡ የሄጎ መሪ የነበረው ማሃድ ሀሰን፣ ሀሰን ዋሊ( የአብዲ ኢሌ የአክስት ልጅ )በተለያዩ የኮንትሮባንድ ስራ የሚታወቀውና የአብዲ ኢሌን ሃብት እንደሚያንቀሳቅስ የሚታወቀው ''SALMA GROUPE” ባለቤት አህመድ ሃጂ ሀሰን ዋል ከፍተኛ ገንዘብ በመመደብ እንዲሁም የቀድሞ ፕሬዝዳንት ከድር መሐመድ መአሊም (የአብዲ ኢሌ የአጎት ልጅ)ን ጨምሮ የተደራጀው ቡድን ምን እየሰራ እንደሆነ ከፀጥታ አካላት አይንና ጆሮ አልተሰወረም፡፡ #አብዲ ጅግጅጋ ወዳሰማራቸው ሰዎች በመደወልና ገንዘብ በመላክ በቅርቡ ሁሉም ነገር ይሳካል! ይላል። #ዋነኛ የሴራው አካላትም በአብዲ ስለታቀደው የጥፋት ድግስ ፣ እነማን እንዳሉበት፣ ለግዜው ያቀዱት ያልተሰካው አብዲ ደንግጦ መግለጫ በማውጣቱ እንደሆነ፣ እነማንን እንደመለመሉ ጭምር ሲነጋገሩ እያንዳንዷ ንግግራቸው ተደምጣለች። አጃኢብ ነው!!! አብዲ ዛሬም ካለፈው ስህተቱ ሳይማር ከህዝብ የዘረፈውንና በነ አህመድ ሃጂ ሀሰን ዋል (ሰልማ ግሩፕ) ስም የሚንቀሳቀስለት ገንዘቡን እየረጨ ህዝብን ወደ ብጥብጥ ክልሉን ወደ አለመረጋጋት በመክተት ጅግጅጋንና ሶማሌ ክልልን እንደ ሃምሌ 28 በደም አበላ ለማጠብ ከግብረ አበሮቹ ጋር ደፋ ቀና እያለ ይገኛል፡፡ #ኧረ_ገና_ብዙ_ጉድ_አለ!!!!! ለክፍል 2 መረጃ እየተዘጋጃችሁ ጠብቁን!!!!!!

Natnael Mekonnen

21,775 просмотров • 1 год назад

እኔ በግሌ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ Abiy Ahmed Ali 🇪🇹 መሠረተ ልማት ባይገነባ ሀገር ባያለማ ከጠዋት እስከማታ ቢያሻው እግሩን ሰቅሎ ቢፈልግ ጋደም ብሎ የሚውል መሪ ቢሆን እንኳን እንደነዚህ ያሉ ገሚሱ በኦሮሞ በትግራይ እና በአማራ ሕዝብ ጫንቃ ታዝሎ ገሚሱ በኢትዮጵያዊነት ለምድ ተጀቡኖ የነበረ እና አሁንም እያላዘነ ያለውን አለሌ የስልጣን ጥመኛ ሁላ ለምዳቸው ተገፎ የጎጠኝነት ዛራቸው ተንገፍግፎ ተራግፎ አደባባይ እርቃናቸውን አጥቦ ጨምቆ ስላሰጣልን እና ኢትዮጵያን እና ሕዝቧን እንደራስ ቅማል ተጣብቀው ደም የሚጠቡበትን በር ስለነፈጋቸው ብቻ እስከቀራንዮ እደግፈዋለሁ ። ነገሩ ግን ሰውየው (አቢቹ) Office of the Prime Minister - Ethiopia ልማቱንም እንክርዳድ ከስንዴ እየለዩ ሀገር ማጥራቱንም ከቴክኖሎጂው እስከ ዲፕሎማሲው እያሳለጠ እና በዐይነት በዐይነቱ እያቀላጠፈው እንኳን እዬዬን የትግል ስልት ላደረገው ጥራዝ ነጠቅ መርህ አልባ ተቀዋሚ ለደጋፊዎቹም የቱን ተናግረን የቱን እንደምንተው ግራ እስኪገባን ድረስ ከአቅማችን በላይ ሆኖብናል ትንግርቱ! ወንበር ያፅና ብለናል‼️ ግን ግን ጀዌ ቀዌ Jawar Mohammed ምነው Tsegaye Ararssa Hᴇɴᴏᴋ G. Gᴀʙɪsᴀ ህዝቅኤል ጋቢሳ ምናምን የከሸፈው የናይሮቢው the so called የመፅሀፍ ምርቃት ፕሮግራምህ ላይ ጋብዘህ አዳዲሶቹን cheerleaderችህን Neamin Zeleke Mesay Mekonnen Andargachew Tsege ደረጄ ሀብተወልድ Dereje Habtewold እና መሰል የ ደረት ደቂዎቹን ማህበራት (ወ.ሸ.ፋ) ዎችን ዘነጋሀቸው? ሰብሰብ ብሎ ለመላዘኑ ጥሩ አጋጣሚ ነበር እኮ 🤔 ከኑማ‼️ #Ethiopia 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

Kiya Negash /ታይሲ/ የ ኢትዮጵያ ካድሬ🇪🇹🇪🇹🇪🇹

23,024 просмотров • 1 год назад

ስሩና አሳዩኝ? ስልጣን ልቀቅና እናሳይሀለን። ለነገሩ ኢኮኖሚ እንዴት ማሳደግ እንደሚቻል መለስ ዜናዊ አሳይቶህ አልነበር እንዴ? ጤነኛ መሪ በአንተ ቦታ ቢሆን ኖሮ፣ አንተ ለጦርነት ያባከንከውን 60 ቢሊዮን ዶላር (30 ትግራይ፣ 10 አማራ እና 20 ኦሮሚያ) እንዲሁም እንደ ህፃን በብልጭልጭ ላይ ያባከንከውን 2.5 ትሪሊዮን ብር ለሚሊዮኖች የስራ እድል የሚፈጥሩ፣ የውጪ ምንዛሬ ወጪን በመቀነስ እና ገቢን መጨመር የሚያስችሉ፣ ወሳኝ መሰረተ ልማቶች፣ የግብርና እና ኢንዱስትሪ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ፕሮጄክቶች ለመስራት ያስችሉ ነበር። ለምሳሌ በመለስ ታቅደውና ተጀመረው የነበሮ ፕሮጄክቶችን፣ አንተ እንዲቆረጡ በማድረግ ገንዘቡን ለጦርነትና ብልጭልጭ መጫወቻእዎች ያዋልከውን እንይ። ማዳበሪያ ፋብሪካዎች * ያዩ ፣የሚፈጀው ገንዘብ 540 ሚሊዬን ዶላር ፣ 120 ሚሊዬን ዶላር ከወጣበት በኋላ ነው የተቋረጠው * ዲረ ዳሞ፡ 2.4 ቢሊዮን * አጠቃላይ የሚይስፈልገው ገንዘብ 3 ቢሊየን ገደማ ነው። የስኳር ፋብሪካ * ኦሞ-ኩራዝ ( አምስቱን ፋብሪካዎች)፦ ሊገኝ ይችል የነበረው ምርት 1.4 ሚሊዬን ቶን፣ የሚፈጀው ወጪ 3.8 ቢሊዬን ዶላር ነበር። ሶስቱ ፋብሪካዎች ተቋረጡ፤ሁለቱ በመለዋወጫ እጦች 35% ያክል ብቻ እየሰሩ ነው። * ከሰም፦ ሊገኝ የሚችል ምርት 120,000 ቶን፣ ግንባታው የሚፈጀው ገንዘብ 460 ሚሊዬን ዶላር፣ ከመለዋወጫ እጦት የተነሳ በ 40% ብቻ እያመረተ ነው። * ተንዳሆ፦ ሊገኝ የሚችለው ምርት 618,000 ቶን፣ የሚፈጀው ገንዘብ 720 ሚሊየን ( 700 ሚሊየን ከወጣበት በኋል የተቋረጠ) * በአጠቃላይ እነዚህን የስኳር ፋብሪካዎች አጠናቆ በሙሉ አቅም ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስፈልገው ገንዘብ 5 ቢሊዬን ገደማ ነው። የባቡር መንገድ * አዲስ አባባ -ጂማ-ደምቢ-ዶሎ- ጋምቤላ ( 4.2 ቢሊዬን) * አዲስ አበባ-ሃዋሳ-ሞያሌ ( 3.1 ቢሊዬን) * አዋሽ -ሃራገበያ- መቀሌ ( 1.6 ቢሊየን_ * ከፊንፊኔ -ባህርዳር- መተማ ( 3.6 ቢሊዬን) * እንዚህን ባቡር መንገዶች አጠናቆ ሙሉ ለሙሉ ወደ ስራ ለማስገባት የሚስፈልገው ገንዘብ 12.5 ቢሊየን ነው። እነዚህ አብይ ያስቆማቸውን ወሳኝ መሰረት ልመቶች እና ፋብሪካዎች ለመገነባት በአጠቃላይ የሚያስፈልገው ገንዘብ 20 ቢሊየን ዶላር ገደማ ነው። እንዚህ ፕሮጄክቶች ቢጠናቀቁ ኖሮ በብዙ ሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ ዜጎች የስራ እድል ይፈጥራሉ፣ ብዙ ቢሊየን ዶላር የውጪ ምንዛሬ ያስገኙ ነበር። አቢይ በሀገር ገነዘብ እቃእቃ ሲጨወት ከርሞ ማፈር ሲገባው አይኑን በጨው ታጥቦ ሊኩራራ ይሞክራል! የአንድ ሀገር መሪ ሀላፊነት ሰፈር እየመረጡ ብልጭልጭ ማብራት ዛፍ ላይ እየጠመጠሙ አብሮ ፎቶ መነሳት አይደለም። የሀገር መሪ ሀላፊነት በእውቀት ላይ የተመሰረተ የኢኮኖሚ ፖሊሲ እና እቅድ ማውጣት፣ ብቃት ያላቸውን ሃላፊዎችን መልምሎ እንዲያስፈፅሙ ማሰማራት፣ ተፈጻሚነቱን በየጊዜው በመከታተለ እና በመገምገም ግድፈቶች ካሉ ማስተካከያ አቅጣጫ ማስቀመጥ ነው።

Jawar Mohammed

60,000 просмотров • 1 год назад

ነሃሴ 2016 አብይ አህመድ በገዛ ወሬው የስከረ መሪ። የሚገርም ዘመን፣ ከዋናው የሃገር መሪ እስከ ተራው ካድሬ ምንም አይነት የሞራል ኮምፓስ የሌላቸው፤ የሞራል ልጓማቸው የተበጠሰባቸው ሆነዋል። የኢትዮጵያ ጉዶች ። እንዳንዴ ለእነዚህ ሰዎች አጓጉል ንግግር መልስ መስጠት እንደነሱ መሆን ነው በሚል ስጋት ዝምታ መምረጣችን የራሳቸውን ቅጥፈት እንደእውነት በመውሰድ በእብደት ህዲድ እንዲነጉዱ ከማድረጉ በላይ የእነሱን መበጥረቅ (ከኮሜዲያን እሸቱ መለስ የተማርኩት ዘመኑን የዋጀ ቃል) ጥቂቶችንም ቢሆን ማወናበዱ ስለማይቀር፣ ሁሌም ባይሆን አልፎ አልፎ የተመዘነና በቅጡ የታሰበበት ምላሽ መስጠት ተገቢ ሆኖ አግኝቸዋለሁ። ለዚህ ነው እየታከተኝም ቢሆን አልፎ አልፎ ብእሬን የማነሳው። 1. ሀተታ ላለማብዛት አጠቃላይ ከሆነው የሃገር ሁኔታ ልጀመር፤ “ኢትዮጵያ ብሄራዊ ደህንነቷን እና ጥቅሟን የሚያስጠብቅላት መንግስት የላትም። መንግስቷ በአንድ በራሱ ምስል በስከረና ባበደ አደገኛ ግለሰብ እጅ ወድቋል። ይህ በራስ ምስል አምልኮት የአእምሮ በሽታ የተጠቃ ግለሰብ ከኢትዮጵያ ጫንቃ ላይ ካልተነሳ ኢትዮጵያና ህዝቧ ብሄራዊ ደህንነታቸው፣ ጥቅማቸው፣ ሰላማቸው ብልጽግናቸው አይረጋገጥም ስንል ዝም ብለን እንደ አብይ አህመድ፣ እየተበጠረቅን አይደለም። ኢትዮጵያ መሬት ላይ ያለውን ሃቅ መሰረት አድርገን ነው። አብይ አህመድና ደንገጡሮቹ ግን ይህ ማየት ከማይችሉበት የተዘጋ የአእምሮ ውቅር ወይም ህሊና ገንብተው ተቀምጠዋል። መስማት ብቻ የሚፈልጉትን እየሰሙ፣ ማየት ብቻ የሚፈልጉትን እያዩ፣ ማመን ብቻ የሚፈልጉትን እያጠለሉ እያመኑ እንዲኖሩ ያደረገ፣ እውነታን በካደ የቅዥተ አዙሪት ውስጥ ወድቀዋል። እንደማይሰሙን ብናውቅም እስኪ ጥቂት እንበላቸው። ዝምታችን ለእብደታቸው የራሱን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ መፍቀዱ እኛንም ተባባሪ ያደርገናልና። የአንድ ሃገር ብሄራዊ ደህንነት ጥቅም የሚከበረው በመከላከያ ሰራዊቱ ነው። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ሰራው ዳር ድንበርና ሉአላዊነት ማስከበር መሆኑ ቀርቶ የአንድ ግለሰብ ስልጣን ለማስጠበቅ ሲል ከመላው የሃገሪቱ ህዝብ ጋር ተራ በተራ ወይም በአንድ ጊዜ ሲዋጋ መኖር፤ የገዛ የሃገሩን ልጆች መግደልና በነሱም መገደል እጣው ከሆነ ሰነበተ። ኢትዮጵያ በሁሉም አቅጣጫ ዳር ድንበሯ ተደፍሮ፣ መሬቷ በውጭ ሃሎች እጅ ተይዞ ይህን ማስቆም የሚገባው የመከላከያ ተቋም መሳሪያውን፣ የሰው ሃይሉንና መሉ ጉልበቱን በኢትዮጵያውያን ፍጅት የአንድን ግለሰብ የስልጣን ሱስ ለማርካት በስራ ላይ እንዲያውል ተደርጓል። የሰራዊቱ ጄነራሎች ለዚህ ታማኝነታቸው ቢሸጡት እስከ 500 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ መሬት ታደሏቸዋል፣ የሃገር ወርቅ ከየክልሉ መሪዎች ጋር በመሻረክ እያስቆፈሩ ከሃገር ውጭ ያወጣሉ፣ መሳሪያና መረጃ ለአልሸባብ ሳይቀር ይሸጣሉ፣ የግንባታ የንገድ ድርጅቶች፣ ከህንዶችና ከቻይኖች ጋር አቁመው ከሪል እስቴት አለፈው መለስተኛ ግድቦች ይገነባሉ። ለመከላከያ ከተመደበው ግዙፍ ባጀት የሚዘርፉትን እዚህ ላይ ማከል ነው። ሌላው የአንድ ሃገር የብሄራዊ ደህንነትና ጥቅም አስከባሪ ተቋም፣ የመረጃ የደህንነት ተቋሙ ነው። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ደህንነት ተቋም እንደተቋም መስራት ካቆመ ሰንብቷል። በሃሰት የትወልድ፣ የትምህርትና የማነንት መታወቂያ ማስረጃ፣ በዘመድ አዝማድ፣ በምልጃና በጉቦ የሚቀጥራቸውን ሰዎች እውነተኛ ማንነት መስሪያ ቤቱ ከማያውቅበት ደረጃ ላያ ደርሷል። ግለሰቦች በጠላት ሃገራት መንግስታትና ድርጅቶች ተመልምለው፣ በተቋሙ ውስጥ መተከላቸውን ወይም ከሰራተኞቹ መሃል ለጠላት ተመልምለው የሚሰሩ ከሃዲዎች እንዳይኖሩ የሚከታተል፣ በደህንነቱ መስሪያ ቤት ላይ የስለላ ስራ የሚሰራ ጸረ መረጃ የተባለው ክፍል ከደህነነት ተቋሙ ከጠፋ ስንብቷል። በዚህም የተነሳ አልሸባብ ወኪሎቹን በኢትዮጵያ የመረጃ መስሪያ ቤት አስቀጥሮ መረጃ መዝረፍ የቻለበት ሁኔታ ተከስቷል። ከመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች መሃል ምን ያህሉ አሁንም ለኢትዮጵያ ጠላቶችና መረጃ ለሚፈለጉ ሌሎች ተቋማት እንደሚሰሩ፣ መረጃ እንደሚሸጡ አይታወቅም። የመረጃ መስሪያ ቤቱ ከሱማሌው አልሸባብ እስከ ናይጀሪያው ቦኮ ሃራም አባላት የኢትዮጵያን ፓስፖርት በማደል በሃሰተኛ ስምና መረጃ በኢትዮጵያ ፓስፖርት በአለም ላይ መንቀሳሰ የሚችሉበትን ሁኔታ ፈጥሯል። ቀደም ብሎ ይደረግ የነበረው ሳምንታዊ፣ ወርሃዊ፣ የግማሽ መንፈቅ የመረጃ መስሪያ ቤቱ ግምገማዎች አይደረጉም። እቅዶችም የሉም። የሃገር አደጋ ትነተና አይቀርብም። የመረጃ ስራ የ24 ሰአታት ስራ መሆኑ ቀርቶ እንደማንኛውም መስሪያ ቤት ከሰአት በኋላ የስራ ሰአት 11 አንድና 12 ሰአት ላይ ሲያበቃ አብሮ ይቆማል። ከተማውና ሃገሪቱ በምሽት ያለደህንነት መስሪያ ቤቱ ክትትልና ቁጥጥር አድረው ይነጋላቸዋል። ሲመሸ የደህንነት መስሪያ ቤቱ የስራ ድርሻ በየጭፈራ ቤቱ እየዞሩ ባለቤቶቹን እያስፈራሩ መጠጣትና እንደማፍያ አለቆች የከለላ ክፍያ (protection fee) መሰብሰብ ሆኗል። የመስሪያ ቤቱ አለቆች በከፍተኛ ደረጃ የሚናናቁ፣ እርስ በርሳቸው የማይነጋገሩ፣ ሁሉም በግልና በቀጥታ ለእብዱ ጠቅላይ ሚኒስቴር ወሬ አቀባዮች ሆነዋል። የመስሪያ ቤቱ ሃላፊዎች ሙሉ ጊዚያቸውን እንደ መከላከያ ጀነራሎች በግል ሃብት ማካበቺያነት፣ የሃገርና የህዝብ ሃብት ዘረፋ ላይ የሚያወሉ ሆነዋል። ይህን የሚያደርጉት ደግሞ ልክ እንደ ወታደራዊ ጀኔራሎች በአለቃቸው በአብይ አህመድ እየታወቀ ነው። ታማኝ እስከሆኑ በየትኛውም የዘረፋ ስራ እንዲሰማሩ ፈቃድ ሰጥቷቸዋል። በርካታ ማስረጃዎች አሉን። ሌላው የሃገር ደህንነት ጠባቂ ተቋም የፌደራል ፖሊስ ተቋም ነው። ይህ የፌደራል ፖሊስ ተቋም እየከረረ በሄደ የዘር ክፍፍል የተወጠረ፣ ተቋማዊ አንድነቱ የተናጋ ነው። በዚህም የተነሳ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው በተለይ የአማራ ተወላጅ አባላቱ (የትግራይ ሰዎች ከመስሪያ ቤቱ ውስጥ ከጠፉ ቆይቷል) መሳሪያቸውን እንደያዙ የሚከዱበት ሁኔታ የተስፋፋበት ተቋም ነው። መሪዎቹ ከአደገኛ እጽ አንስቶ እስከ ከፍተኛ የኮንትሮባንድ ንግድ ውስጥ የተደፈቁ መሆናቸው ተደጋግሞ የተገለጸ ጉዳይ ነው። ባለፈው ሳምንት አብይ አህመድ ኮማንደር ፍቅሩ አለማየሁ ለሚባል የአዳነች አበቤ አጃቢ ለነበረ ግለሰብ በቀጥታ በምክትል ኮሚሽነርነት ማእረግ የአዲስ አበባ የወንጀል መከላከል ሃላፊ እንዲሆን የስጠው ሹመት “የዘር ኮታ ምደባውን የተጻረረ፣ የአማራን ቦታ ለኦሮሞ የሰጠ ነው” በሚል በተቀሰቀሰ ቁጣ 16 ዝቅተኛ መኮንኖችና ፖሊሶች እኛን አማሮችን በእዚህ ተቋም ውስጥ የሚወከለን የለም በሚል ምሬት መሳሪያቸውን ይዘው መሰወራቸው ታውቋል። የፌደራል ፖሊሲ ሃላፊዎች ዋናው ስራቸው በአብይ አገዛዝ ላይ ህዝብ እንዳያማጽ ከመጠበቅ ውጭ በሃገር ብሄራዊ ጥቅምና ደህነት ዙሪያ ከታዬ ዋናዎቹ የሃገር ጠንቆች ከሆኑ ሰነባብቷል። ሌላው የሃገር ጥቅምና ደህነነት ማስጠበቂያ ተቋም የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱና የዲፕሎማሲ ስራው ነው። ይህን መስሪያ ቤት በአብይ ተላላኪዎች ከመሞላት አልፎ የአብይ አህመድ የግል ፍላጎት ማስፈጸሚያ ከሆነ ቆይቷል። ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከታዬ አጽቀስላሴ በላይ ተሰሚነት ያላት ምክትሉ ብርቱካን አያና ናት። አምባሳደሮች የሚያደገድጉት፣ የተሻለ ምደባ እንዲያገኙ ጉቦና ስጦታ የሚሰጡት ለዚች የአብይ አህመድ የቅርብ ሴት ነው። የአብይ አህመድ እብደት በሚገባ የተገለጸበት፣ የሃገርና የህዝብ ደህንነትና ጥቅም ከፍተኛ አደጋ ላይ የወደቀበት የመንግስት እንቅስቃሴ ቢኖር የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ ነው። በተሳሳተ የአብይ አህመድ የውጭ ጉዳይ እንቅስቃሴዎች ኢትዮጵያ ከሁሉም ጎረቤቶቿ ጋር ተጣልታለች። ማንም በበጎ አይን የሚያያት የለም። ምንም ደሃ ብትሆን በቀጠናውና በአለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎምሲ መስኩ ትታይበት የነበረው የላቀ ስፍራዋ ላይ ዛሬ የለችም። ኢትዮጵያ ለደረሰባት ጉዳት ብዙ ምሳሌ ማቅረብ ቢቻልም ከሱማሌላንድ ጋር አብይ ገባሁ ያለው በቅጥፈት የተሞላ፣ ገና ከመጀመሪያ የትም እንደማይደርስ የተነበይነው የመግባቢያ ሰንድ ፊርማ ትልቁ ምሳሌ ነው። ሰነዱ በተፈረመበት ወቅት “ለሃገር ደህንነት አደገኛ ውሳኔ ነው” ብለን የተቃወምነው ግለሰቦች፣ አብይና አሽቃባጮቹ እንዳሉት ሃገር ሲያልፍላት አይናችን የሚቀላ ባናዳዎች ስለሆን አልነበረም። ይህን የሚሉት የባንዳነት ታሪክ በዘር ማንዘራችን እንደሌለ አጥተውት አይደለም። የሱማሌን ሉአዋላዊ ሃገርነት የሚጻረር ድርጊት በኢትዮጵያ ላይ ብዙ መዘዞች ያስከትላል ከሚል ተጨባጭ ስጋት በመነሳት ነበር ስምምነቱን ያወገዝነው። ለአንድ ሰሞን ህዝብን የማወናበድና የማፋዘዝ ፕሮጀክት ሲባል የተፈጸመ ድርጊት ኢትዮጵያ ሰራዊቷን ከሱማሌያ የምታስወጣበትን፣ አልሸባብ ኢትዮጵያ ድንበር ላይ ካምፕ የመሰረተበትን፣ ግብጽ በኢትዮጵያ ድንበር ሱማሌ ውስጥ ወታደሮቿን ማስፈር፣ የሱማሌን ሰራዊት ማሰልጠን የምትችልበትን፣ ቱርክ የሱማሌን የባህር ዳርቻዎች ደህንነት የምትጠብቅበትን ውሎች ከሶማሊያ ጋር መዋዋል የቻሉበትን ሁኔታ መፍጠር ችሏል። ህዝብ ለህዝብ መቀራረብ ጀመሮ በነበረው የኢትዮጵያና የሱማሌ ህዝብ ግንኙነት ላይ ያደረሰው ጉዳት ቀላል አይደለም። የመከላከያ የደህንነት ተቋማቷን አፍርሳ የተቀመጠችው ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲ መስኩ የሃገሪቱን ጥቅም ተጻረው ለሚቆሙ ሃገራትና መንግስታት፣ እድሜ ለአብይ አህመድ፣ የተመቻቸ ሁኔታ ፈጥራ አርፋዋለች። ሌላው የአንድ ሃገር ሉአላዊነት፣ደህነነትና ጥቅም ማስከበር የሚችለው ሃይል ከህዝብ አንድነትና በህዝብና በመንግስት መቀራረብ የሚገኘው ጉልበት ነው። የአብይ አህመድ አገዛዝ ሆን ብሎ የሃገሪቱ ህዝቦች እርስ በርስ በጎሪጥ እንዲተያዩ፣ ከዛም አልፈው እንዲጨፋጨፉ የሚሰራ መንግስት ሆኗል። በአብዛኛው የሃገሪቱ ህዝብ ላይ ጦርነት ከፍቶ ተጋጭቷል። አሁንም እየተጋጨ ነው። ከጦርነት በተረፈው ህዝብ ላይ የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሚል ስም የኢኮኖሚ ጦርነት ከፍቶ፣ ከጥቂት ባላሃብቶችና የመንግስት ባላስልጣናት በቀር የእያንዳንዱን ዜጋ ህይወት የምድር ሲኦል አድርጎት አርፏል። አብይ በፈጸማቸው ዘርፈ ብዙ ጸረ ህዝብ ድርጊቶቹ ከህዝብ ጋር ሆድና ጀርባ ሆኗል። ከሃገሪቱ የቆዳ ስፋት የሚቆጣጠረው እየጠበበ ሄዶ አገዛዙ እንደለቡ ያሻወን መፈጸም የሚችልበት ቦታ አዲስ አበባ ላይ ብቻ ሆኗል። አብይ አህመድ ህዝብንም ከሃገር ደህንነትና ጥቅም ማስጠበቅ ስራ አግሎታል። ኢትዮጵያ አደገኛ ሁኔታ ውስጥ ናት የምንለው ይህን ሁሉ ጉድ አይተን ነው። 2. ወደ ውቅታዊ ጉዳይ ስመለስ አብይ አህመድ የጫካ ቤተመንግስት፣ የኮሪደር ልማት፣ አዲስ ቱሞሮ (ጥራዝ ነጠቅ ስትሆን የሚመጣ የእንግሊዝኛ አጠቃቀም) እያለ የአልሞትኩም ብዬ አልዋሽም ፕሮፓጋንዳውን እራሱ እየሰራ፣ እራሱ እየተጋተ ሰከሮና ደንዝዞ መኖርን መርጧል። ይህን ድርጊቱን አያዋጣም የምንለውን በወሬ የምንኖር እራሱን በስራ የሚኖር አድርጎ መግለጽ ደግሞ የሰሞኑ የፐሮፕጋንዳ አቅጣጫው ሆኗል። ከዚህ ቀጥሎ የምላቸው ጥቂት ቃላቶች የአብይ አህመድ የሰሞኑ ጭኸቶች የቁራ ጭኸቶች እንደሆኑ የሚያሳዩ ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያልገባው እሱ የያዘው ስልጣን በአንዳንዶቻችን እጅ ቢገባ ለጫካ ቤተመንግስቱ አዲስ አበባ ላይ የሚያጠፋውን ከ10 እስከ 15 ቢሊዮን የሚደርስ ዶላር ከሱ በተሻለ ሃገርና ህዝብን ወደከፈተኛ ብልጽግና መውሰድ የሚያስችል ስራ ማዋል የሚችሉ ልጆች ኢትዮጵያ እንዳሏት ነው። አብይና አሽቃባጮቹን በምክን ያት ተከራክሮ ማሳመን እንደማይቻል በገባንም በህዝብ ፊት ማሳፈር ስለሚቻል 10 ቢሊዮን ዶላሩን እንዴት እንደምናጠፋው ቀጥሎ እናቀርባለን። 10 ቢልዮን ዶላሩን ምን እናደርገው እንደነበር ስንነግራችሁ የጫካው ቤተመንግስት፣ በግንባታ ወቅት የሚቀጥረውንና ከተገነባ በኋላ ስራ የሚፈጥርለትን የሰው ብዛት፣ ግንባታው ሲያልቅ የሚያስገኘውን የኢኮኖሚ ጥቅምና ሃገራዊ ፋይዳ በሚገባ ተመልክተን ነው።ዝርዝሩን ማቀረብ ያለበት አብይና ኩባንያው ነው። እኛ ማድረግ የምንችለው እንዲህ አይነቱ የጫካ ቤተመንግስት ኢንቨስትመንት ቱሩፋቶቹ ምን ይሆናሉ ብለን በመገመት ብቻ ነው። በተለይ ይህን ያህል ዶላር የፈሰሰበት ቤተመንግስት ሰላምና መረጋጋት በሌለበት ሃገር ቀርቶ ሰላም ቢኖርም ክወጭ የሚስበው ጎብኝ ይሁን በዚህ ቤተመንግስት ዙሪያ የሚገነቡ ህንጻዎች የሚስቡት የውጭ ኢንቨስትመንት እዚህ ግባ የሚባል የኢኮኖሚ ፋይዳ እንደማይኖር የታወቀ ነው። በግንባታ ስራውም ሆነ ካለቀ በኋላ የሚፈጥረው የስራ እድል ውሱን ነው። እንግዲህ ይህን አይነቱን በሃገራችን ከሚሰሩ ስራዎች ቅደም ተከተሉ እጅግ የተዛናፈን የዛሬ መቶ አመት እንኳን ሊሰራ የማይገባውን ስራውን እያመላከተ ነው አብይ አህመድ የስራ ሰው መሆኑን ሊነግረን የሚዳዳድው። እኛ ደግሞ ይህን በጫካ ቤተመንግስት ላይ አብይ አህመድ የሚያወጣውን ከ10 እስከ 15 ቢሊዮን ዶላር፣ በ10 ቢሊዮን ዶላር ገድበን ይህን ገንዘብ በሀሃገራችን ውስጥ ቅድሚያ ማግኘት አለባቸው ከምንላቸው ስራዎች አንዱ በሆነው የማዳበሪያ ኢንደስትሪ ምስረታ ላይ እንዴት እንደሚውልና ምን ሃገራዊ የኢኮኖሚ እርባና እንደሚኖረው በማሳየት አብይ የወሬ እንጂ የስራ ሰው አለመሆኑን ማሳየት እንችላለን። የማዳበሪያ ኢንደስትሪ ራሳችንን በምግብ ለመቻል፣ ከዛም አልፎ ግብርናውን መሰረት ያደረገ የኢንዱስትሪ አብዮት ለማስጀመር፣ በግብርና ምርታቸን ላይ የተመሰረተ የውጭ ምንዛሪ ችግራችንን መቅረፍ የምንችልበት እድል ለመፍጠር፣ በግንባታው ወቅትና ከተገነባ በኋላ የሚቀጥረውን የቋሚ ሰራተኛ ብዛት፣ ኢንዱስትሪው ራሱ የሚያመርተው ምርት ከሀገር ውስጥ ፍጆታ ተርፎ ወደ ውጭ ከሚላከው ምርት የሚገኘውን የውጪ ምንዛሪ ገቢ በአንድ ላይ ግምት ወስጥ አስገብተን የአብይን 10 ቢሊዮን ዶላር በማዳበሪያ እንዱስትሪ ምስረታ ላይ ብናውለው ምን ውጤት እናገኝ ነበር የሚለውን ጉዳይ ለአብይ አህመድና በዙሪያው ላሉ አሽቃባጮቹና በቅርቡ አዲስ አበባ ከተማን እናስውባለን በሚልፕሮፓጋንዳቸው ሊያደነዝዙት የፈለጉትን ህዝብ የሚከተሉትን ሃቆች እንንገራቸው። አብይ አህመድ ጫካ ቤተመንግስት የሚገነባባትን ገንዘብ ወደ ማዳበሪያ ኢንደስትሪ አዙሮት ቢሆን። 1. ለማዳበሪያ መስሪያ አስፈላጊ የሆነወን አሞኒያ የተባለ ኬሚካል በአመት በብዙ ሚሊዮኖች ሜትሪክ ቶን ማምረት ይቻል ነበር። 2. ለማዳበሪያ መስሪያ አስፈላጊ የሆኑትን ፎስፌትና ፖታሸ 1 እስከ 2 ሚሊየን ሚትሪክ ቶን በአመት ማምረት ይቻል ነበር። 3. ይህ የማዳብሪያ ኢንደስትሪ ኢትዮጵያ በአመት ለማዳበሪያ የምታወጣውን ከ800 ሚሊዮን እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ያሰቀር ነበር። 4. በውጭ የማዳበሪያ ኩባንያዎችና መጓጓዣዎች እንዲሁም በየጊዜው ከሚዋዥቅ የማዳባሪያ ዋጋ ራሷን ነጻ ማድረግ ትችል ነበር። 5. ዘመኑ የሚፈቅደውን የተራቀቀ ቴክኖሎጂ በማደበሪያ ማምርቻ ስራ ላይ ማዋል ትችል ነበር። 6. ይህ ዶላር በጥናትና ምርምር ላይ የተመስረተ ከማዳበሪያ ጋር የተያያዘ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የጥናትና የምርምር ተቋም እንዲኖረን ያስችል ነበር። 7. ለተፈጥሮ እና ለአካባቢ ጥበቃ እንብካቤ የሚያደርግ ኢንደስትሪ መገንባት የሚያስችል አቅም ይሰጠን ነበር። 8. በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞች፣ ኤንጂኔሮች፣ ኬሚስቶችም የፋብሪካ ማሽነሪ አንቀሳቃሾች፣ የማእድን ሰራተኞች፣ የድጋፍ ስራ የሚሰሩ ሌሎችንም በመቶ ሸዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች ስራ ያስገኝ ነበር። 9. የማዳበሪያው ኢንደስትሪ ትልቅነት የአለምን የማዳበሪያ ገበያ ከ5 እስከ 15 በመቶ የመቆጣጠር ትልቅ አቅም ሰለሚኖረው ኢንቨስትመንቱ ከኢትዮጵያ ውጭ በሌሎች ሃገሮች ሳይቀር መስሪያ ቤቶች የሚኖሩትና ሰራተኞችም የሚቀጥር ይሆን ነበር። 10. ኢትዮጵያ ለማደባሪያ መስሪያ የሚሆን ትልቅ የፖታሽ ክምችት ቢኖራትም፣ ለፖታሽና ለሌሎችም ለማዳበሪያ መስሪያ የሚሆኑ ወሳኝ ግብአቶችን ሩቅ ሳትሄድ ከጎረቤቶቿ ማግኘት የምትችልበትን የኢኮኖሚ ትብብር እድል የሚከፈት ይሆን ነበር። ከኤርትራና ከጅቡቲ ጋር ፎስፌትና ፖታሽ በማውጣት፣ ከደቡብ ሱዳን እና ከሱዳን ናይትሮጂን ለሚያስፈለገው የአሞኒያ ማዳበሪያ ለመስሪያ የሚሆነው የተፈጠሮ ጋዝ በመግዛት የሚፈጠረው የኢኮኖሚ መደጋገፍ ለቀጠናው ትልቅ ትርጉም ይኖረው ነበር። 11. ጥናቶች የሚያሳዩት በ10 ቢሊዮን ብር ኢንቨስትመንት የሚጀመር የማዳበሪያ ኢንደስትሪ ስራው ተጠናቆ በሙሉ አቅሙ ማምርት ሲጀመር ከ 5 ቢሊዮን እስከ 15 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ አመታዊ ገቢ ሊኖረው የሚችል ይሆናል፣ ከዚህ ውስጥ ትርፉ በየትኛውም ኢንደስትሪ ከሚገኝ ትርፍ የላቀ እንደሚሆን ይገመታል። 12. ይህ ስራ ለማስጀመር • የአሰሳና የአዋጭነት ጥናት ለማጥናት ከ50 እስከ 100 ሚሊዮን ዶላር፤ • የመስረተ ልማት ስራ ትልቁ ነው። የማእድን ማውጫ መሳሪያዎች፣ የማጓጓዣ ስራ፣ የኤነርጂ አቅርቦት፣ የውሃ አቅርቦት ስራ ከ500 ሚሊዮን እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ወጪ እንደሚኖረው ይገመታል። • ማእድን ማውጣትና ማጣራት ማምረት ፋብሪካዎችን ማቆም ከ 1 ቢሊዮን እስከ 2 ቢሊዮን ዶላር እንደሚፈጅ ይገመታል። • ለሎጂስትክ ለሃገር ውስጥና ወደ ውጭ ማጓጓዣ ከ300 ሚሊዮን እስከ 500 ሚሊዮን ዶላር፤ • አመታዊ የሰራተኛ ደሞዝ፣ የጥገና የመለዋወጫና ሌሎችም ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ መንቀስቃሰ እሰክሚችል ድረስ የሚያፈልገው ወጪ ከ 200 እስከ 500 ሚሊዮን ዶላር ይሆናል። አጠቃላይ የአንድ ትልቅ የማዳበሪያ ፋብሪካ የኢንቭስትመንት ወጪ ከ2 ቢሊዮን ዶላር እስከ 4 ቢሊዮን ዶላር እንደሚደርስ ይገመታል። ስራው አድካሚ ነው። በትንሹ አምስት አመታት ጊዜ ይወስዳል። እንደ ኮሪደር ልማት፣ እንደ ጫካ ፕሮጀክት በአዲስ አበባ ቤተመንግስቱ አካባቢ ለአብይ አይን ማረፊያነት የሚሰራ አይሆንም። አብይ ጠዋትና ማታ የሚጎበኘው፣ ውጤቱም በሚብለጨጩ ህንጻዎች በቀላሉ የማይታይ ስራ ነው። እንግዲህ ይህ ቁልፍና መሰረታዊ የሆነ የሃገርና የህዝብ ትልቅ ችግር ለመቅረፍ የሚያስፈለግ፣ ከዛም አልፎ በየአመቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ማስገኘትና ከፍተኛ ቁጠር ያለውን ቋሚ ሰራተኛ ለመቅጠር የሚያስችል አንድ የማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ከ 2 እስከ 4 ቢሊዮን ዶላር የሚጠይቅ ከሆነ፣ የጫካው ቤተመንግስት በሚሰራበት በ 10 ቢሊዮን ዶላር በአማካይ 3 ትልልቅ የማዳበሪያ ኢንዱስትሪዎች መገንባት ይቻል ነበር ማለት ነው። ይህን ኢንደስትሪ ለጫካው ከሚወጣው ወጪና የጫካው ፕሮጀክት ለሃገርና ለህዝብ ከሚሰጠው ፋይዳ ጋር ማነጻጸሩና የፋይዳወን ልዩነት የመገመቱ ስራ ለብልሁ የኢትዮጵያ ህዝብ እንተወዋለን። የአብይ አህመድ አገዛዝ የሀገር ጠንቅ ነው። ብልጭልጭ ፕሮጀክቶቹም የግለሰቡን ብኩን ስብእና የሚያሳዩ ናቸው የምንለው፣ በበልጽግና ዙሪያ አብይ እንደሰበሰባቸው የፓርቲው ደናቁርትና እነሱን እንዲያጅቡ አብይ ስልጣን ያጋራቸው እንደብርሃኑ ነጋ እንደ ግርማ ሰይፉ እንደነ በለጠ ሞላ ከአብይ እግር ስር እየወደቀን ጭራችንን የማንቆላው፣ በዘራችሁ አይድረስ ከሚል የመዋረድ እርግማንም ራሳችንን የምናድነው ጌታቸውና ፈጣሪያቸው አብይ እንደሚለው በወሬ ስለምኖር ሳይሆን፣ ለግል ስማችን፣ ክብራችንና ሆዳችን ሳይሆን ሃገርን የሚጠቅምና የሚጎዳ ተግባር ምን እንደሆነ ስለምናውቅ ነው። ይች በድህነት የተጨማደደች ሃገራችን እና በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠረው ደሃ ህዝባችን ወደ ብልጽግና የሚያመራው ጥቂት ከተሜዎችና ዳያስፖራዎች፣ አብይ እንዳለው ፎቶ መነሳት የሚችሉባቸውን ቦታዎች አዲስ አበባ ላይ ለመፍጠር ሲባል ብዙ ቢሊዮን ዶላሮችን በከንቱ በማባከን እንዳልሆነ ስለምናውቅ ነው። የከተማወን ህዝብ ረሃብ ለማስታገስ ማዳበሪያ ያለውን ትርጉም ስለምናውቅ ነው። ልኡላዊነትን አሳልፎ የሸጠ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ስራ ላይ እንዳናውል የሚያደርገንን፣ ከፍተኛ የሆነ የወጭ ምንዛሪ ፍላጎታችንን የሚቀንስ፣ ኢንደስትሪው ተጨማሪ የውጭ ምንዛሪ የሚያስገኝልን እንደሆነ ስለምናውቅ ነው። ግብርናን መሰረት ያደረገ የኢንደስትሪ አብዮት በማካሄድ አስተማማኝ ልማት ለህዝባችን ማጎናጸፍ እንደሚችል ስለሚገባን ነው። የአብይ አገዛዝ ያለበት ችግር በእውነት፣ በሃቅ፣ በእውቀት ላይ ተመስርተው ስካርና እብደቱን ከሚያመላክቱት ሰዎች ይልቅ እሱ የሚለውን እንደገደል ማሚቱ የሚያስተጋቡ፣ ወይም ለመጀመሪያ ጊዜ ከወንድ ጓደኛዋ ጋር እንደተዋወቀች አይና አፋር ለጃገረድ የሚሽኮረሞሙ ወራዶችን ማቅረቡ ነው። ከእነዚህ ሰዎች መሃል እኔ በግሌ የማውቃቸው በአንድ ወቅት ትልቅ ክብርና ግምት የሰጠኋቸው ሰዎች መገኘታቸው ነው፤ “እንዲህ አይነት ውርደት በዘራችሁ አይድረስ” እንድል ያሰኘኝ። አንዳርጋቸው ጽጌ Abiy Ahmed Ali 🇪🇹 FDRE Government Communication Service Mustafe M. Omer Al Ain Amharic አል ዐይን አማርኛ Ethiopian Reporter Sahle-Work Zewde Reuters Ethiopian Citizens for Social Justice #Ezema FDRE Ministry of Justice ኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር Al Jazeera English Billene ቢልለኔ Aster Seyoum Neamin Zeleke Office of the Prime Minister - Ethiopia BBC News (UK) DW Amharic Redwan Hussien Daniel Kibret Taye Atske Selassie Ethiopian National Dialogue Commission VOA Amharic Fana Media Corporation S.C. (FMC) @walta_info EBC WORLD እስከዳር እምሻው 🇪🇹አስካለ ማርያም Dawit

Andargachew Tsege

61,317 просмотров • 1 год назад

አብይ አህመድ “ይሉሽን በሰማሽ ገበያ ባልወጣሽ” የሚለውን አባባል አያውቀውም መሰለኝ? አብይ አህመድ፣ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስቴር፣ እሮብ እለት ጥቅምት 18 2018 በኢትዮጵያ ተወካዮች ምክር ቤት ውስጥ፣ ለምክር ቤቱ አባላት ጥያቄዎች መልስ በመስጠት ሰበብ ካደረገው ዲስኩር መሃከል፣ ብዙ ትችትና ውግዘት ሊሰጡባቸው የሚችሉ በርካታ ጉዳዮች እንዳሉት ይታወቃል። በርካታ ሚድያዎች ብዙዎቹን ጉዳዮች እያነሱ እያፍተለተሏቸው ይገኛሉ። እዚህ ላይ እኔ ትኩረት ከማደርግባቸው ነጥቦች መሃል አንዱ አብይ አህመድ ስለባንዳነት ስለከሃዲነት ባደረገውና እጅግ ባስገረመኝ ዲስኩር ላይ። ይህ ብቻ አይደለም። የግል ጉዳይም አለኝ። ሌላው ደግሞ አብይ አህመድ በዚህ እለት ንግግሩ “ጉልበታቸው መዛሉን እድሜያቸው መግፋቱን ያልተገነዘቡ ካገር ወጥተው በለመዱት የመቃወምና የመላላክ መንገድ ቀጥለውበታል” ብሏል።፣ አብይ አህመድ ይህን ሲል ስሜን በቀጥታ አልጠቀሰም። ባይጠቅስም አብይ ግራዋ እንደጋቱት ሰው በዚህ መንገድ እየተንገፈገፈ ሊናገራቸው የሚችሉ በርካታ አዛውንቶች በውጭ እንደሌሉ አውቃለሁ። ይህ ብቻ ሳይሆን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር እንዳበቃ፣ ራሱ ያደራጀው የሚድያ ስራዊት፣ የአብይን ንግግር ሲያብራራ፣ በምሳሌነት እንዲያቀርብ የተነገረው እኔን መሆኑን ማወቅ ስለቻልኩ ንግግሩ እኔን የሚመለክት ለመሆኑ ጥርጣሬ እንዳይኖረኝ አድርጎታል። የዲጂታል ሚድያውም የተሰጠውን ተልእኮ ተቀብሎ የሚችለውን ሁሉ እየሰራ ነው። ለማንኛውም ይህ የአብይ እዲጂታል ሰራዊቱድርጊቶች ደህና አርፎ የነበረውን ብእሬን እንዳነሳ ያደረጉኝ ጉዳዮች እነዚህ ናቸው። አብይ አህመድ የሚባል አምባገነን፣ ለባንዳነትና ለክሀደት፣ የተመቻቸ የአእምሮ ውቅር፣ የማንነት ሃረግ፣ የታሪክ መስረት ያለው ሰው መሆኑ ይታወቃል። የእወቀትና የልምድ ውሱንነት ያለው መሆኑ ከራስ መተማመን ማነስ የሚመነጭ ለባንዳነትና ለተላላኪነት በቀላሉ የሚያጋልጠው ተፈጥሮ ያለው ሰው ያደርገዋል። በተግባርም፣ ደግሞ ዳጋግሞ ሃገርን፣ ህዝብን፣ ወዳጆቹን፣ ቅርቦቹን፣ እውቆችን የካደ ሰው ነው። ታዲያ እንዴት ሆኖ ነው እንደዚህ አይነት ፍጥረት በድፍረት ስለክህደት፣ ስለባንዳነትና ስለቃል ማጠፍ፤ የሞራልና የስብእና ልእልና ያለው ሰው ይመስል በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ዲስኩር ለመስጠት የደፈረው። የሚመልስልኝ የለም ብሎ? ነገሩ ሁሉ አንቺው ታመጭው ስልሆነ እስኪ አናሩጠው። አብይ አህመድ የኤመሬቱ ገዥ የመሃመድ ቢንዛይድ ጀለቢያ ውተፍ ነቃይና ተላላኪ መሆኑ ይታወቃል። አብይ ከመሃመድ ቢንዛይድ መመሪያ ይቀበላል፣ ቀጠናው በመሃመድ ቢንዛይድ ትእዛዝ ይበጠብጣል። ኢትዮጵያን የመሃመድ ቢንዛይድ የፖለቲካ ሺሻ ማጨሻ እቃ ካደረጋት ስንብቷል። ከእርግዝና መከላከያ ጋር የተያያዘውን ሌላ ቃል ያልተጠቀምኩት፣ የአንባቢን ስሜት ላለመንካት ነው። አብይ “ለአሜሪካ ስሰልል ነበር፣ ዛሬም ቢሆን ለአሜሪካ ራሴን እሰዋለሁ” ብሎ በአደባባይ ለጋዜጠኛ ለመናገር የደፈረ የመጀመሪያው የአንድ ልኡዋላዊ የሆነ ሃገር መሪ ነው። የመጨረሻውም ሳይሆን አይቀርም። በተላላኪነትና በባንዳነት መሰለፍን፣ መለመንን ለምኖ ምጽዋት ማግኘትን ልዩ ጸጋ እና ችሎታአድርጎ የሚመለከት ሰው ነው። ራሱን አዋርዶ ኢትዮጵያን የሚያክል ትልቅ ሃገር ያዋረደ ግለሰብ ነው። ይህ ግለሰብ ሌሎችን በባንዳነት ሲከስ፣ በተላላኪነት ሲወነጅል ትንሽ አፉን ያዝ አያደርገውም። የሃገሬ ሰው “ተናግሮ ከሚያናግር ይሰውርህ” ይላል። ይህ ምርቃት ስላልደረሰኝ ለእዚህ አብይ አህመድ ለሚባል ደፋር፣ "ቃል መጠበቅ ፣ አለመክዳት፣ ባንዳና ተላላኪ አለመሆን" ማለት በተግባር ሲገለጥ ምን እንደሚመስል እሱ ራሱ ከሚያውቃቸው ሃቆች በመነሳት ትምህርት መስጠት ተገቢ ሆኖ አግኝቸዋለሁ። ከታች የምታይዋቸው የቪዲዮ ክሊፖች አንዱ፤ የመጀመሪያው አብይ አህመድ “ አንተ ካልተፈታህ ስራዬን እለቃለሁ ብዬ አስፈታሁ” ብሎ ቢሮው ጠርቶ ባነገረኝ (በኋላ ውሸት መሆኑን አረጋጫለሁ) እለት፣ ከአራት አመት እስራት በኋላ ከእስር በተለቀቅኩ ማግስት፣ ግንቦት 22 2010 ቀን የተናገርኩት ነው። ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስና የቻይና ሚድያ (CGTN) በእንግሊዝኛ ቋንቋ የሰጠሁት ቃለ መጠይቅ ነው። ትርጉሙ፤ “የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር፣ ለመቀራረብና ለመደማመጥ የሚያበረታታ ነው። እውነተኛ ለሆነ የፖለቲካ መስተጋብር ግን በርካታ ነገሮች መስተካከል አለባቸው። ተጨባጭ የሆኑ ስራዎች መሬት ላይ መሰራት አለባቸው። የፖለቲካን እስረኞችን መፍታት ብቻ በቂ አይደለም። ጥሩ ንግግር ማድረግ ብቻ በቂ አይደለም። እዚህ ሃገር ውስጥ፣ በፖለቲካው፣ ተጨባጭ ከሆኑና መሰራት ካላባቸው ጉዳዮች ውስጥ የነጻና ገለልተኛ ተቋማት የመቆማቸው ጉዳይ ወሳኝ ነው። በሌሎች የማህበራዊና የኢኮኖሚ ዘርፎችም መቃለል የሚጠይቁ ችግሮች አሉ። እኛ የመቃወም ሱስ የለብንም። የምንቃወም ክሆነ፣ መቃወም የሚጠይቁ ጉዳዮች ስላሉ ብቻ ነው። ለመቃወም ብቻ ስንል አንቃወምም። አወንታዊ ጉዳዮች ካሉ የማናመሰግንበት/የማናደንቅበት ምክንያት የለም። በጎ ያልሆኑ ነገሮች ከተከሰቱ፣ አፋኝነት ከመጣ ከህዝብና ከሃገር ጥቅም ጋር የሚጻረሩ ስራዎች ከተሰሩ መቃወም ብቻ ሳይሆን አምረን የምንቃወም ይሆናል። ለሁሉም መልካም ጅማሮ ነው።” የሚል ነው። ከዛን እለት ጀመሮ በግሌ ለአብይ አህመድ በቀጥታ በዋትስአፕ ቻት፣ በሰነዶች፣ በአካል በተገናኘንባቸው በርካታ አጋጣሚዎች በጎና በጎ ያልሆኑ አመለካከቶቹን እና ድርጊቶቹን ያለምንም አድርባይነት ለመጠቆም ሞክሪያለሁ። ሁሌ አሉታዊ ትችቶችን ማቅረብ ብቻ አይደለም። በጎ ጅማሮች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማበራታት ሞክሬያለሁ። በድጋፍም ደረጃ ቢሆን አብይ አህመድ ቀጣፊ መሆኑን ሳልረዳ፣ እንደ ታዬ ደንዳ አይነቶቹ ስለስሜን እዝ መጠቃትና በጥቃቱ የአብይ ሴራ ምን እንደነበር ሳይነግሩን፣ ወያኔዎችን ሙሉ በሙሉ ወንጀለኛ አድርጌ በማየት፣ የአብይ መንግስት በወያኔ እንዳይሸነፍ ከጎኑ ቆሜ ድጋፍ ሰጥቸዋለሁ። በተኙበት ወያኔ ጨፈጨፋቸው ተብሎ ለተነገሩን የሰራዊቱ አባላት ቤተሰቦች መቋቋሚያ መጽሃፍ ሸጬ ካገኘሁት ገንዘብ ላይ 100 ሸህ ብር ለግሻለሁ። ይህ የአብይ አህመድ ሰራዊት ግን ዛሬ በአማራ ክልል የልጆቻችንን የእህቶቻችን ጡት ይቆርጣል። ይህ እንዳለ ሆኖም በበኩሌ በ2010 አ.ም “የመቃወም ሱስ የለብንም የሚለውን አባባሌን ከሚገባው በላይ በመለጠጥ ድጋፍ መስጠት ሊቋረጥ የሚገባበትን ወቅት ማየት እንዳልችል ባደረገ ሆደ ሰፊነት ለአብይ መንግስት ድጋፍ እንደሰጠሁ የሚያሳይ ነው። ቃል መጠበቅ ይህ ነው። በተለጠፈው ቪድዮ ላይ “መንግስት ማፈን ከጀመረ፣ የህዝብን እና የሃገርን ጥቅም ተጻሮ የሚቆም ከሆነ መቃወም ብቻ ሳይሆን አምረን እንቃወመዋለን” ብዬ ነበር። ነገሮች እየተበላሹ ሲመጡ፣ የደህነነት ቀውሱ እየጨመረ፣ አፈናው፣ እልቂቱ፣ መፈናቀሉ እየተበራከተ፤ ዘረፋው እየተስፋፋ፣ መንግስት ለማይፈጽማቸው ሃላፊነቶቹ የሚሰጣቸው ሰበቦችና ምክንያቶች አጠራጣሪ መሆን ሲጀመሩ፣ “ይህ መንግስት የከፋ አገዛዝ ወደመሆን እያኮበኮበ ነው” የሚል ስሜት ሲቀሰቅስብኝ፣ ምልከታዬን በውስጥ ማቅረብ ይሻላል” በሚል ብዙ ነገሮች እንዲታረሙ ተቃውሞዬን በቀጥታ ለአብይ አህመድ አቅርቤያለሁ። ሆኖም ግን ይህ በውስጥ የሚቀርብ ምልከታ ለአብይ አገዛዝ የተመቸው እንደሆነ፣ ሰውየው በአንድ ጆሮ ሰምቶ በሌላው የሚያፈሰው መሆንን መረዳት ስጀመር፣ በአደባባይ በበርካታ መድረኮች፣ የአገዛዙን አደገኛ አካሄድ በንግግር በጽሁፍ ተችቻያለሁ። ሁለተኛው ቪዲዮ 2013 አልቆ 2014ን ለመቀበል በተዘጋጀ በአል ላይ የተናገርኩትና በኢሳት ቴሌቪዥን ለህዝብ የተላለፈ ነው። ንግግሩ በቀጥታ የሚመለከተው፣ በኦሮሞ ብልጽግና ባለስልጣናትና የቅርብ ደጋፊዎቻቸው ዘንድ እየተስፋፋ የመጣውን የተረኛነት ስሜትና፣ የዘር የስልጣን እና የጥቅም ትስስር፣ በከተማው ውስጥ እየታየ ከመጣው አይን ያወጣ ዘረኛነት ጋር ተያይዞ ያደረግሁት ነው። የሙስናው ጉዳይም ከመቼው ዘመን በከፋ መልኩ ስር እየሰደደ እንደሆነ መረጃ በማሰባሰብ ላይ ተመስርቼ የተናገርኩት ነው። ሁሉንም ጽሁፌን ንግግሬን ከማንም አስቀድሜ ለአብይ አህመድ እንዲደርሰው ሳደርግ ነው የኖርኩት፤ አላየሁትም እንዳይል። አሁንም ይህ በሁለተኛው በቪዲዮ ያቀረብኩት ንግግር በ2010 ከእስር በተፈታሁበት ቀን ካቀረብኩት ንግግር ጋር ማነጻጸር ይቻላል። “የምንቃወመው ዝም ብለን ለመቃወም አይደለም፣ መቃወም የሚያስፈልጉ ጉዳዩች ሲኖሩ ነው” ላልኩት ማረጋገጫ ነው። ይህ ንግግር ትልቅ የተቃውሞ ንግግር አልነበረም። በወቅቱ ማንንም ሰው ይህን ንግግር፣ ዝቅተኛው በመንግስት ላይ ሊቀረበ የሚችለው ትችት እንደሆነ የሚገንዘብ ይመስለኛል። ከዚህ ንግግር ውጭ በርካታ በሚገባ የተጻፉ ትችቶቼን በፌስ ቡክ ገጾች በየጊዜው አደባባይ አውጥቻለሁ። የመጨረሻውና በተፈታሁ እለት የተናገርኩትን “አፋኝ እና ጸረ ህዝብና ጸረ ሃገር ተግባራት መንግስት ከፈጸመ አምረን እንታገለዋለን” ያልኩት ደረጃ የደረሰ ጉዳይ መምጣቱን የሚያሳየው ነጥብ ነሃሴ 17 2015 አ.ም. የአብይ አህመድ አገዛዝ የአማራን ክልል በወታደራዊ እዝ አገዛዝ ስር ያስገባበትን አዋጅ ተከትሎ የጻፍኩት ነው። በፌስ ቡክ “ መሆን የነበረበት ወያኔን ጠበቅ አማራን ለቀቅ ማድረግ ነበር” በሚል ርእስ ከጻፍኩት የተወሰደ ነው። “በአማራ ክልል እየሆነ ባለው እጅግ አሳዛኝ ሁኔታ ላይ የዛሬውን የግል ምልከታዬን ሳቀርብ ከላይ በአንቀጽ 5 እና 6 ገደብ የሌለው (በእለቱ የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እያጣቀስኩ ነው) ስልጣን የተሰጣቸው አካላት በእኔም ይሁን ከእኔ ጋር ቅርበት ባላቸው አካላት ላይ ማንኛውንም እርምጃ ሊወስዱ እንደሚችሉ እያወቅሁ ነው። በሌሎች ግለሰቦች ላይ እንዲህ አይነቱ እርምጃ እየተወሰደ እንደሆነ መረጃው እየደረሰኝም ነው (እስራት፣ አፈና ድብደባ ማለቴ ነበር)። በእንዲህ አይነቱ ወቅት ዝምታን ያልመረጥኩት፣ በመንግስት ወንጀለኛ ሆኖ ከመታየት ይልቅ በራሴ ህሊና ወንጀለኛ ሆኖ መታየት የበለጠ የሚያስጨንቀኝ ሰው በመሆኔ ብቻ ነው። ከጥቂት ቀናት በፊት ጌታቸው ረዳ፣ ዴንቨር ኮለራዶ ላይ ከ200 ሽህ በላይ ለውጊያ የተዘጋጀ ሰራዊት እንዳለው ተናግሯል። በዚህ ሰራዊት የተማመነው ጄነራል ጻድቃን "የማእከላዊ መንግስቱ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ቃል በገባልን መሰረት የትግራይን ግዛቶች ማለትም ወልቃይትን እና ራያን የማይመልስን ከሆነ በጉልበት እናስመልሳለን" ብሎ እዛው አሜሪካን ውስጥ በተዘጋጀ ስብሰባ ላይ ተናግሯል። ጻድቃን “ቃል ተገብቶልናል” ስለሚለው ጉዳይም ይሁን ስለጉልበት መጠቀሙ የሚናገራቸው ነገሮች ዝም ብሎ እንዳልሆነ ከህወሃት ከራሱ ስናገኛቸው የነበሩ በቂ መረጃዎች እንዳሉ የመንግስት ባለስልጣናት ያውቁታል። እነዚህ ሁለት ግለሰቦች ከየትኛውም የወያኔ አመራር በተለየ በጦርነቱ ወቅት “ከአማራ ህዝብ ጋር ሂሳብ እናወራርዳለን” በማለት በአደባባይ የተናገሩ ፣ የአማራ ህዝብ የተጨፈጨፈበትን፣ ሰው ብቻ ሳይሆን እንስሳቱ በጥይት የተቆሉበትን፣ ክልሉ ከስልጣኔ ርቆ ወደ ድንጋይ ዘመን እንዲመለስ ተደርጎ የመሰረተ ልማት ግንባታዎቹ፣ የህዝብ የአገልግሎት ተቋማቱ እንዲወድሙ የተደረገበትን፣ የፕሮፓጋንዳና የጦር እስትራተጂ የነደፉና ያስፈጸሙ ናቸው። (አንባቢ ይህን ሃቅ ዛሬ ጌታቸውና ጻድቃን የት እንዳሉ ራሱን እየጠየቀ እንዲያየው ያስፈልጋል) የሚገርመው ግን የታሪክ ቧልት የሚል ትርጓሜ ሊያሰጠው በሚችል ደረጃ፣ ጌታቸውና ጻድቃን፣ የአንደኛ ደረጃ የአውሮፕላን ቲኬት ተቆርጦላቸው፣ ሲኦል ድረስ ወርደንም ቢሆን እናወድመዋለን ባሉት የኢትዮጵያ መንግስት፣ የቪአይፒ እንክብካቤ ተደርጎላቸው ወደ አሜሪካ ተጉዘው፣ በከፍተኛ እብሪትና መንደላቀቅ ስለሰራዊታቸው አቅምና ስለቀጣይ ጦርነት፣ ስለትግራይ አሸናፊነት በአሜሪካን ከተሞች ሲደሰኩሩ፣ ሲዘፍኑ፣ እስክስታ ሲወርዱ፣ ከሀገር ያሸሹትን ሃብት (ይህ ጻድቃንን እንጂ ምሽኪኔታን ጌታቸውን አይመለከትም) ቦታ ቦታ ሲያስይዙ፣ ከአሜሪካን መንግስት ጌቶቻቸውና እመቤቶቻቸው (ከነሱዛን ራይስ ) ጋር ሴራ ሲሸርቡ ከርመው በክብር ወደ መቀሌ ተመልሰዋል። በሌላ በኩል እነዚህ ግለሰቦች በአሸናፊነት ስሜት መናገሻ ከተማቸው በገቡ በቀናት ልዩነት፣ የእነዚህን እብሪተኞች ሃገር የማፍረስ ተልእኮ በመመከት፣ በስልጣን ላይ ያለውን መንግስት መንበር በማጽናት፣ በተኛበት ለተጨፈጨፈው የሃገር መከላከያ ሰራዊት አለኝታ በመሆን፣ በንብረቱ፣ በደሙና በአጥንቱ በህይወቱ መስዋእትነት የከፈለው የአማራ ህዝብ በወታደራዊ አገዛዝ ስር እንዲወድቅ ተፈርዶበታል። ይህን ካልኩም በኋላ ጽሁፌን የደመደምኩት እንዲህ ብዬ ነበር። “አሁን በአማራ ክልል ከልዩ ሃይሉ መፍረሰ ጋር ተያይዞ የተፈጠረውን ችግር ፣ ወያኔዎች ሲያደርጉ እንደኖሩት፣ የክልሉን መሪዎች በስልጣን እና በጥቅም በመደለል፣ ህዝቡንም ሆነ አንዳንዶቹን ከህዝቡ ጎን ለመቆም የወሰኑትን የአስተዳደርና የጸጥታ አካላት በማስፈራራት፣ ወይም ከእውነታው ጋር በተጣላ የፕሮፓጋንዳ ውርጅብኝና (በወረዳ ሶስት ሽፍቶች የሚለውን የሰሞኑን የአብይ አባባል ልብ ይሏል) በሌሎችም ዘለቄታዊ መፍትሄ ማምጣት በማይችሉ መንገዶች ሄዶ ለማቃለል የሚደረግ ሙከራ የትም እንደማያደርስ መታወቅ ይኖርበታል።” በመጨረሻም የሚያዳምጥ ካለ፣ “እንዲህ አይነት ችግር በኢትዮጵያ ውስጥ ሲከሰት የመጀመሪያው አይደለም። የመጨረሻውም ላይሆን ይችላል። እንዲህ አይነት፣ በተለይ ከእውነተኛ የህዝብ ብሶት ጋር የተያያዙ ችግሮች ሲፈጠሩ፣ ችግሮቹን ለመፍታት በተለያዩ ዘመናት ያለፉ መንግስታት ከሄዱበትና ውጤት ካላመጡ አደገኛ አካሄዶች መማር ተሸናፊነትን ሳይሆን ብልህነትን የሚያሳይ ይሆናል።” እላለሁ። ይህ ጽሁፍ በተጻፈ በ15ኛው ቀን፣ ኢትዮጵያን ለቅቄ፣ ንብረትም መኖሪያ ቤትም ወደ አልነበረኝ እንግሊዝ ሃገር ጉዞየን ጀመርኩ። ለማጠቃለል አብይ እንደሚለው ሳይሆን፣ እኔ አቅሜ መዛሉንም፣ እድሜየ መግፋቱን የጠፋኝ ሰው አይደለሁም። ችግሩ እኔ አቅሜን ካላማወቄ ጋር የተሳሰረ ሳይሆን ከራሱ ከአብይ የአመለካከት ችግር ጋር የተይያዝ መሆኑን መረዳት አልቻለም። ማንም ሰው ሺ ጊዜ ጉልበቱ ቢዝል፣ እድሜው ቢገፋ በምርጫው ካልሆነ በቀር፣ ለአብይ ባሪያ ወይም ገረድ ሆኘ ከመቅረት የሚያድነው አቅም ሁሌም እንደሚኖረው አብይ ማየት አልቻለም። አብይ አህመድ፣ ሁሉም ሰው በየጊዜው ሰበብ እየፈጠረላቸው እንደሚስድባቸው እንደ ብርሃኑ ነጋ፣ እንደ አርጋዊ በርሄና እንደ ቀጀላ መርዳሳ ይመስለዋል። እብይ ነው በምሳሌነት የሚያነሳቸው እኔ አይደለሁም። “ጉልበቴ ዝሏል። እድሜ እየገፋ ነው። አብይ ለምን ሚሊዮኖችን አይገድልም፣ አያፈናቅልም፣ አያሳድድም፣ ለምን እስር ቤቶች በንጹሃን እስረኞች ሞልተው አይተርፉም። ለምን ሃገር እስከ አጥንቷ በዘራፊዎች አትጋጥም። ለምን መቶ ሺ እናትችና እህቶች አይደፈሩም። ለምን የሴቶች ጡት አይቆረጥም፣ ህጻናትና አረጋዋያን አይጨፈጭፍም። ምን አገባኝ።” ብለው የተስጣቸውን የስልጣን እና የጥቅም ፍርፋሪ እየለቀሙ መኖር የማይችሉ አዛውንቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ አብይ ለመረዳት ስሪቱ ሊፈቅድለት አልቻለም። የአብይ አህመድ መሰረታዊ የፖለቲካ ፍልስፍና በጥቅምና በስልጣን የማይደለል ሰው አይኖርም ነው። “እርካብና መንበር” የሚል ርእስ የሰጠው መጽሃፉ፣ አብይ ዛሬ የሚያደርጋቸውን ድርጊቶቹን የቀረጹትን አስተሳሰቦቹን በሚገባ ዘርዝሮ ያስቀመጠበት ዋናው መጽሃፍ ነው። "መደመር" አይናችሁን ጨፍኑና ላሞኛችሁ በሚል ስሌት የተጻፈ ቅጥፈት ነው። "ስልጣን እና ጥቅም፣ የአንቱታ፣ የትልቅነትና የአዋቂ ነዎት ፉገራ የማያታልለው ሰው የለም" የሚል እምነቱን አብይ አህመድ በዚህ መጽሃፉ ውስጥ ደግሞ ደጋሞ ያቀረበው ጉዳይ ነው። አብይ ይህን እምነቱን አድማሳዊ እውነት አድረጎ የተቀበለ ሰው ነው። አብይ ይህን ሁሉንም ሰው “በሬ ሆይ እያልኩ ስልጣን እና ጥቅም እያሳየሁ ባሪያ አደርግሃለሁ” በሚል የያዘውን ጽኑ የፖለቲካ እምነት የሚጻረር የሰዎች አቋም ሲያጋጥመው እንደ ግራዋ ይመረዋል። “ማንጎ ነኝ ብለው የሚያስቡ ግን ግራዋ የሆኑ” በሚል ባላፈው እሮቡ በፓራማ ስብሰባው ወቅት ግራዋ እንደጋቱት ሰው ተንገፍግፎ የተናገረበት ምሬት ምንጩ ይህ ብቻ ነው። ይህን ስል እኔ ማንጎ ነኝ እያልኩ እንዳልሆነ ይታወቅልኝ። Abiy Ahmed Ali 🇪🇹 AA. PROSPERITY PARTY Neamin Zeleke Dawit እስከዳር እምሻው 🇪🇹አስካለ ማርያም Ephrem Madebo Elizabeth Altaye @yeabatuli

Andargachew Tsege

11,759 просмотров • 8 месяцев назад